የዕቃዎች ሽያጭ ጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 15/2018
በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በህገ ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀሱ ተይዘው የተወረሱ አዲስ ብትን ጨርቅ እና የተሸከርካሪ መለዋወጫ ዕቃዎች ለ 3ተኛ ጊዜ ጨረታ የወጡ፣ የቤት መገልገያ ዕቃዎች ለ 2ተኛ ጊዜ ጨረታ የወጡ እንዲሁም ሌሎች ዕቃዎች ባሉበት ሁኔታ በግልፅ እና በሃራጅ ጨረታ አወዳድሮ መሽጥ ይፈልጋል፡፡
1. በመሆኑ ቅ/ጽ/ቤቱ ባወጣው የዕቃ ሽያጭ መወዳደር የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የጨረታ መስፈርቶች የሚያማሉ ተጫራቾች በጨረታው መሳተፍ የሚችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
ሀ) በዘርፉ የፀና ንግድ ፍቃድ ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርቲፍኬት እና የዘመኑን ግብር የከፈለ ለመሆኑ ከግብር ሰብሳቢ መ/ቤት የተሰጠ የምስክር ወረቐት /ክሊራንስ/ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዞ በፖስታ በማሽግ ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖሩበታል ፡፡
ለ) የዚህ አንቀጽ ፊደል ተራ (ሀ) ድንጋጌ ቢኖሩም ግምታዊ ዋጋ ከብር 500ሺ በታች የሆነ ማንኛውም ዕቃ ለመግዛት የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርቲፊኬት ማቅረብ አያስፈልግም ፡፡
2. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱ ዘወትር በስራ ሰዓት ከሰኞ እስከ ዓርብ እና ቅዳሜ ከ2፡00 ሰዓት እስከ 6፡00 ሰዓት የማይመለስ ብር 100/አንድ መቶ ብር/ በኢትዮጵያ ንግድ በሒሳብ ቁጥር 1000012078537 በመክፈል ደረሰኝ ከጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 104 እንዲሁም የጨረታ ሰነድ ቢሮ ቁጥር 411 በመምጣት ይህ ማስታወቂያ አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ እስከ ሰኔ 22/2018 ዓ.ም ድረስ ዘወትር በስራ ሰዓት በአካል በመሄድ ሰነዱ መግዛት ይቻላሉ፡፡
3. ተጫራቾች ለጨረታ የቀረቡትን ዕቃዎች ዝርዝር ጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ አስከ ሰኔ 22/2018 ዓ.ም ይህ ማስታወቂያ አየር ላይ ከዋለበት ሰኔ 16 ቀን 2018ዓ/ም ጀምሮ የሚቆጠር አስከ ሰኔ 22 ቀን 2018 ድረስ ለጨረታ የቀረቡ ዕቃዎች ናሙና በጽ/ቤቱ የሚገኙ መጋዝኖቻችን በአካል እየሄዱ መመልከት ይችላ
4. ግልፅ ጨረታው ጨረታው የሚካሄደው ሰኔ 22 ቀን 2018ዓ/ም ከቀኑ 7፡30 (ሰባት ሰኣት ከሰላሳ ዲቂቃ ) ተዘግቶ በዕለቱ ከቀኑ 7፡45 ( ሰባት ሰኣት ከአርባ አምስት ደቂቃ ) የሚከፈት ሲሆን ሓራጅ ጨረታው ደግሞ ከ8፡00 ጀምሮ ይካሄዳል፡፡
5. ተጫራቾች በግልጽ ጨረታ ለሚወዳደርባቸው ዕቃዎች የሰጡትን ዋጋ አምስት በመቶ(5%) እንዲሁም ለሃራጅ ጨረታ ለመለዋወጫ ዕቃዎች ብር 100,000 እና ለቤት ዕቃዎች 10,000 እንዲሁም ለእርሻ ዕቃወች ብር 5,000 የጨረታ ማስከበሪያ በቅ/ጽ/ቤቱ ስም ETHIOPIA customs commission mekelle branch office በሚል በባንክ አሰርተው ማስያዝ ይጠበቅባችል።
6. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በቅ/ፅ/ቤቱ የመሰብሳብያ አደራሽ 4ተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 401 ይካሄዳል፡፡
7. ተጫራቾች ያስያዙት የጨረታ ዋስትና የጨረታ ውጤት በተገለጸው በ3 (ሰሶት) ቀናት ውስጥ ተመላሽ ይደረግላችዋል፡
8. የጨረታው አሸናፊ ጨረታውን ለማሸነፉ ከተገለጸለት ጊዜ ጀምሮ 5(አምስት) ቀናት ውስጥ ያሸነፈበት ዕቃ ዋጋ ገቢ በማድረግ ዕቃውን መረከብ አለበት፡፡
9. ከላይ በተ/ቁ 9 በተገለጹት ቀናት ውስጥ ክፍያውን ገቢ ያላደረጉ እና ንብረቱን ተረክበው ያልወሰዱ ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት ዋስትና ለቅ/ጽ/ቤቱ ገቢ ሆኖ ዕቃው በድጋሜ ለሽያጭ የሚቀርብ ሲሆን ነገር ግን የዕቃው ዋጋ ገቢ አድርጎ ዕቃው በሁለት ወር ውስጥ ካልወጣ ለንብረቱ የተከፈለው ዋጋ ለመስሪያቤቱ ገቢ ሆኖ እቃው እንደተተወ ተቆጥሮ በሽያጭ ይወገዳል፡፡
10. በጨረታ የሚሸጠው በተቃሙ ከመወረሱ በፊት የዕቃዉ አስመጪ ፤ ወኪል ባለቤት ወይም ቤተሰብ በማንኛውም መልኩ በጨረታ መሳተፍ አይችልም፡፡
11. ቅ/ፅ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ ሊሰርዝ ይችላል፡፡
ለተጨማሪ መረጃ _ በስልክ ቁጥር ኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት +251342407107 ወይም +251342408513/ በመደወል ተጨማሪ መረጃ ማግኘት የምትችሉ
መመለስ