ለሶስተኛ ግዜ የወጣ የኦዲት ስራ ማስታወቂያ
(Audit Work Bid Invitation Notice For The Third Time)
ዳሉል ትራንስፖርትና ንግድ አክሲዮን ማህበር የ2018 በጀት ዓመት የፋይናንስ መግለጫዎችን (Financial Statements) በውጭ ኦዲተር ለማስመርመር ይፈልጋል።
በዚሁ መሰረት በዘርፉ የተሰማሩ እና ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ሚያሟሉ ህጋዊ የኦዲት ድርጅቶች/ባለሙያዎች በጨረታው እንዲሳተፉ ይጋብዛል፡
1. ተጫራቾች ማሟላት ያለባቸው መስፈርቶች፡-
O በAABE የተሰጠ የታደሰ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ያላቸው እና ሰርቲፋይድ (Certified) ወይም ቻርተርድ (Chartered) የኦዲት ድርጅት የሆኑ።
O የዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የንግድ ምዝገባ፣ የTIN፣ የVAT እና የግብር ክሊራንስ (Tax Clearance) ማቅረብ የሚችሉ።
2. የጨረታ አቀራረብ ሁኔታ፡-
O ተጫራቾች የቴክኒክ (Technical) እና የፋይናንስ (Financial) ሰነዶቻቸውን በተለያዩ ኤንቨሎፕ ታሸገዉ መቅረብ ይኖርባቸዋል።
O ልዩ ማሳሰቢያ ለፋይናንስ አቀራረብ፦ ተጫራቾች የሚያቀርቡት የኦዲት አገልግሎት ዋጋ የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ያካተተ (nclusive of VAT) መሆን አለመሆኑን በግልጽ ለይተው ማስቀመጥ ይኖርባቸዋል፡፡ ስራው ውል ከተፈረመበት ቀን ጀምሮ በ1 (አንድ) ወር ጊዜ ውስጥ መጠናቀቅ ይኖርበታል።
3. የጨረታው ማጠቃለያ ቀናት፡-
ማስታወቂያው የወጣበት ቀን፦ 04/12/2018 ዓ.ም
ጨረታው የሚዘጋበት ቀን፦ ማስታወቂያው በይፋ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ 5 ኛው ቀን ከቀኑ 4፡ዐዐ ሰዓት ላይ ይዘጋል።
ጨረታው የሚከፈትበት ቀን፦ ጨረታው በተዘጋበት ዕለት በ 5 ኛው ቀን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በማህበሩ ዋና ቢሮ ከቀኑ 4፡15 ሰዓት ላይ ይከፈታል።
4. አድራሻ እና ማሳሰቢያ፡-
O አድራሻ፦ [መቐለ/17 ቀበሌ]፣ ባሎኒ ሆቴል ፊት ለፊት፣ የቢሮ ቁጥር 6 ስልክ ቁጥር፦ ስልክ ቁጥር 0914727851 0911215844
O ማህበሩ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
መመለስ