ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
የትግራይ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ በአክሱም ከተማ የሚገኘውን የአክሱም ፅዮን ቤተክርስቲያንን ለመጠገን ስለፈለገ በዚህ ስራ ህጋዊ ንግድ ፍቓድ ያላችሁ ተወዳዳሪዎች እንድትወዳደሩ ይጋብዛል። ተወዳዳሪዎች ሊያሟሉት የሚገቡ ነገሮች
1. የ2018 ግብር የከፈሉና የታደሰ ንግድ ፍቃድ፣ በዘርፉ የአቅራቢነት መለያ ቁጥር /Tin number/፣ VAT ተመዝጋቢ የሆነ፣ ቫት ዲክሌር ያደረገና የአቅራቢነት የምስክር ወረቀት መረጋገጫ የሚያቀርብ።
2. በዚህ መሰረት የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ ከቢሮአችን የግዢ ክፍል ቢሮ ቁጥር 110 ከ ቀን 15/07/2018 ጀምሮ ብር 100.00 በመክፈል መውሰድ ይቻላል።
3. የጨረታ ማስከበሪያ ብር 20,000.00 /ሃያ ሺ ብር/ በሲፒኦ /CPO/ ወይ በስርቲፋይድ ቼክ ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ የሚችል/የምትችል/።
4. ተጫራቾች ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 28/07/2018 ከቀኑ 9፡00 ስዓት ድረስ ከታች በተጠቀሰው አድራሻ ማስገባት አለባቸው ዘግይተው የሚቀርቡ ጨረታዎች ውድቅ ይሆናሉ።
5. ጨረታው የሚከፈተው ተጫራቾች ወይም ተወካዮች በተገኙበት በዚሁ ቀን ጨረታ ሰነዱን በወሰዱበት ቦታ ከቀኑ 9፡30 እሚከፈት ይሆናል።
6. ተጫራቾች የሚጫረቱበትን የጨረታ ሰነድ፣ ዋጋ የተሞላበት ኦርጅናልና ኮፒ ለየብቻው በመለየት ፓስታው ላይ በመፃፍና ማህተም በማድረግ በተናጠል በማሽግ ሁለቱን ፓስታዎች በሌላ የውጭ ኢንቨሎፕ ውስጥ በማስገባት ማቅረብ አለባቸው።
7. ቢሮአችን የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ይሁን በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
8. አድራሻችን በመቐለ ጤና ጣቢያ አካባቢ ፎቶ ደስታ ፊትለፊት የሚገኝ ኣብርሃም ደስታ ህንፃ 1ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 110 ነው፡፡
9. ተጫራቾች ሰነዳቸውን ለጨረታ ተብሎ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ እንዲያስገቡ እናሳስባለን።
10. ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 09-14-76-94-50 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል።
መመለስ