የግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ
የመቐለ ውሃ አገልግሎት ጽ/ቤት ለ2018 በጀት ዓመት የሚያገለግል የውሃ ማጣሪያ ኬሚካል (ክሎሪን)ግዢ አወዳድሮ በግልጽ ጨረታ ለመግዛት ስለፈለገ በጨረታው መሳተፍ ለምትፈልጉ ተጫራቾች ጥሪውን ያቀርባል።
1. የታደሰ ሕጋዊ ንግድ ፍቃድና የአቅራቢዎች መታወቂያ ፍቃድ ያላቸው።
2. ቫት የተመዘገበና የመጨረሻ ወር ቫት ዲክለር ያደረገ ቲን ቁጥር ማቅረብ የሚችሉ።
3. የጨረታው ዶክሜንት የማይመለስ 1000 (አንድ ሺ ብር) በመክፈል መቐለ ውሃ አገልግሎት ጽ/ቤት በመምጣት የጨረታው ዶክሜንት ከደጋፊ ስራ ሂደት ግዢ፣ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ቢሮ ቁጥር G1-02 መግዛት ይችላሉ።
4. ጨረታ ዶክሜንቱ ማስገባት የሚቻለው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 15ኛው ቀን 2018 ዓ/ም 4፡00 ሰዓት ወደ ጨረታ ሳጥኑ ማስገባት ይችላሉ፡፡
5. ጨረታው የሚዘጋው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ 15ኛው ቀን 2018 ዓ/ም 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በእለቱ 4፡30 ተጫራች ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል እሁድ ወይ ሕዝባዊ በዓል ከሆነ ደግሞ ቀጥሎ ባለው ቀን 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በእለቱ 4፡30 ተጫራች ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
6. ሁሉም ተጫራቾች 120,000.00 /አንድ መቶ ሺ ብር/ የጨረታ ማስከበሪያ በጥሬ ገንዘብ በባንክ የተረጋገጠ ቼክ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ጋራንቲ እና በባንክ የተረጋገጠ ሌተርኦፍ ክሬዲት ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል።
7. ተጫራቹ ነጠላ ዋጋና የጠቅላላ ዋጋ በግልጽ ማስቀመጥ አለበት በተጨማሪም በጨረታ ዶክሜንቱ ውስጥ የተዘጋጁት ፎርማት ተሞልተውና ተፈርመው መቅረብ አለባቸው።
8. በዶክሜንቱ ከተሰጠው ስፔስፍኬሽን ውጪ የሚቀርብ ተቀባይነት የለውም።
9. የጨረታው አሸናፊ ውል ማስከበሪያ ካሸነፈው ዋጋ በባንክ የተረጋገጠ ቼክ (CPO) በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ጋራንቲ ዋስትና የውል ማስከበሪያ (Performance bond guarantee) 10% ማስያዝ የሚችልና በ3 ቀን ውስጥ ውል አስሮ በዶክሜንቱ በተጠቀሰው ቀን ንብረቱን ማስገባት የሚችል።
10. በጨረታው ሂደት ጨረታውን ለማዛበት ለማጭበርበር የሞከረ ተጫራች ከጨረታው ውጭ እንደሚሆንና በመንግሥት ግዢ እንዳይሳተፍ ለማድረግ ወደ ክልሉ ፋይናንስና ፕላን ቢሮ ደብዳቤ እንደምንፅፍ
11. ጨረታ ሳጥኑ ከተዘጋ በኋላ የሚመጣውን የጨረታ ዶክሜንት ተቀባይነት የለውም።
12. ጨረታው ፀንቶ የሚቆየው ጨረታው ከተከፈተ ለ40 ተከታታይ ቀናት ብቻ ነው።
13. ጽ/ቤቱ ጨረታው እንደ አስፈላጊነቱ ከእያንዳንዱ ነጠላ ዋጋ በ20% የመጨመር ወይም የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው።
14. የሚቀርበው ጨረታ ዶክሜንት
14.1 ቴክኒካል አንድ ኦርጅናልና ሁለት ኮፒ ሰነድ ለየብቻው አሽጎ ማቅረብ የሚችል እንዲሁም
14.2 ፋይናንሻል አንድ ኦርጅናል ሁለት ኮፒ ሰነድ ለየብቻው አሽጎ ማቅረብ የሚችል መወዳደር ይችላል።
15. ፅ/ቤቱ ጨረታው በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡- ትግራይ መቐለ
ስልክ ቁጥር 0344407335/0914755845
የመቐለ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ጽ/ቤት