የዕቃዎች ሽያጭ ጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 8 /2017
በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን በመቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በህገ ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀሱ ተይዘው የተውረሱ የተለያዩ የምግብ ነክ ዕቃዎች፣ የንጽህና እቃዎቸ የቤትና የቢሮ እቃዎቸ፣ የኮንስትራክሽን ዕቃዎች እና ሎይሎች ልዩ ልዩ እቃዎቸ ባሉበት ሁኔታ ብሓራጅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሽጥ ይፈልጋል፡፡
1) በዚህም ቅ/ፅ/ቤቱ ባወጣው የዕቃዎች ሽያጭ ጨረታ መወዳደር ሚፈልግ ማንኛው ተጫራች
ሀ) በዘርፉ የፀና የንግድ ፍቃድ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርቲፍኬት እና የዘመኑን ግብር የከፈለ መሆኑ ከግብር ሰብሳቢ መ/ቤት የተሰጠ ማስረጃ ኮፒ ማቅረብ የሚችል፡፡
ለ) የዚህ አንቀፅ ፊደል ተራ (ሀ) ድንጋጌ ቢኖርም ለጨረታ የቀረቡ ዕቃዎች ግምታዊ ዋጋቸው 500,000 (ከአምስት መቶ ሺ ብር) በታች ድረስ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ ሰርቲፊኬት ማቅረብ አይገደድም፡፡
2) ተጫራቾች ለሓራጅ ጨረታ የቀረቡትን ዕቃዎች እስከ ጥር 27 ቀን 2017ዓ/ም ዘውትር በስራ ሰዓት ከሰኞ ኞ እስከ ዓርብ እና ቅዳሜ ከ 2:00 እስከ 6:00 የማይመለስ ብር 100(አንድ መቶ ብር) 1 ፉቅ ቢሮ ቁጥር 104 በመክፈል የጨረታ ሰነዱ ከ4ተኛ ፉቅ ቢሮ ቁጥር 411 በመውሰድ የዕቃዎች ዝርዝር መመልከት ይችላሉ፡፡
3) በሃራጅ ጨረታ ለመሳተፍ የሚፈልግ ለምግብ ነክ ብር 150,000(አንድ መቶ አምሳ ሺህ) ፣ ለቤትና ለቢሮ ዕቃዎች እና ለንፅህና ዕቃዎች ለያንዳንዳቸው ብር 15000( አስራ አምስት ሽህ) እንዲሁም ለግብርና እና ለኮንስትራክሽን ዕቃዎች ለያንዳንዳቸው 1000(አንድ ሺ ) ዋስትና CPO በመቐለ ጉምሩክ ቅ/ፅ/ቤት ስም በኢትዮጵያ ንግድ ባን ንያዝ ይኖሩበታል፡
4) ተጫራቾች በሚከተለው የጨረታ ቀናት (ስኬጁል) መሠረት መጫረት ይችላሉ፡
የቅ/ጽ/ቤቱ ስም | የንብረቱ ዓይነት | የጨረታው ዓይነት | የንብረት መመልከቻ ሰነድ ከወሰዱ ቀን ጀምሮ | የጨረታው መክፈቻ ቀን ና ሰዓት | |
---|---|---|---|---|---|
ከ | እስከ | ||||
መቐለ ጉ/ቅ/ጽ/ቤት | የተለያዩ ዓይነት ንብረቶች | ሃራጅ ጨረታ | 19/05/2017 ጀምሮ | 27/05/17 | 28/05/2017 ዓ.ም ከጥዋቱ 3:00 ጀምሮ ይካሄዳል |
5) የጨረታ መክፈቻ ቦታ መቐለ ጉ/ቅ/ጽ/ቤት 4 ፉቅ ቢሮ ቁጥር 401 ጨረታው ተጫራቾች/ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባሉበት ይከፈታል፡፡
6) ለጨረታ አሸናፊዎች ተጫራቾች ለጨረታው ዋስትና ያስያዙት ሲፒኦ ከሚከፍሉት ዋጋ ጋር የሚታሰብላቸው ሲሆን ለተሸናፊ ተጫራቾች ያስያዙት የጨረታ ዋስትና በ3 ቀናት ወስጥ ተመላሽ ይደረግላችዋል፡፡
7) የጨረታው አሸናፊ ጨረታውን ለማሸነፉ ከተገለጸለት ጊዜ ጀምሮ 5(አምስት) ቀናት ውስጥ ያሸነፈበት ዕቃ ዋጋ ገቢ በማድረግ ዕቃውን መረከብ አለበት፡፡
8) ከላይ በተ/ቁ 7 በተገለጹት ቀናት ውስጥ ክፍያውን ገቢ ያላደረጉ እና ንብረቱን ተረክበው ያልወሰዱ ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት ዋስትና ለቅ/ጽ/ቤቱ ገቢ ሆኖ ዕቃው በድጋሜ ለሽያጭ ይቀርባል፡፡
9) ቅ/ፅ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ ሊሰርዝ ይችላል፡፡ ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር ኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ መቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት +251342407107 ወይም +251342408513/ በመደወል ተጨማሪ መረጃ ማግኘት የምትችሉ መሆኑ እንገልፃለን
መመለስ