ኩባንያችን መስፍን ኢንዳስትሪያል ኢንጂነሪንግ ኃላ.የተወ የግል ኩባንያ (FSWEI ኢንድስትሪ) የተለያዪ እቃዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ስለሚፈልግ መስፈርቶች የምታሟሉ ተወዳዳሪዎች እንድትሳተፉ ኩባንያችን ይጋብዛል::

የጨረታ ማስታወቂያ

ኩባንያችን መስፍን ኢንዳስትሪያል ኢንጂነሪንግ ኃላ.የተወ የግል ኩባንያ (FSWEI ኢንድስትሪ) የተለያዪ እቃዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ስለሚፈልግ መስፈርቶች የምታሟሉ ተወዳዳሪዎች እንድትሳተፉ ኩባንያችን ይጋብዛል::

የጨረታ መስፈርት

1. ተጫራቾች በዘርፉ የ2016 ዓ/ም የታደሰ ሕጋዊ የንግድ ሥራ ፈቃድ ያላቸው ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ : የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር እና የወሩ ቫት ማሳወቅያ ፎቶ ኮፒ በማያያዝ ከጨረታው ዝርዝር (ሰነድ) ጋር ማስገባት ይኖርባቸዋል

2. ተጫራቾች የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ 4 የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር እና የወሩ ካት ማሳወቅያ ፎቶ ኮፒ የማይመለስ እና ኦርጅናል የሚመለስ በመያዝ የጨረታ ሰነድ ከቀን 18/07/2024 እ.ኤ.አ ጀምሮ እስከ 23/07/2024 እ.ኤ.አ መቐለ ላጪ ቅርንጫፍ FSWEI ኢንድስትሪ በስራ ሰኣት መወሰድ ይኖርባቸዋል::

3. ጨረታው በ 23/07/2024 እ.ኤ.አ ከቀኑ 8:00 ተዘግቶ በተመሳሳይ ቀን ከሰኣት 8:30 ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው በተገኙበት መቐለ ዋና መስርያ ቤት በሚገኝ FSWEI ኢንድስትሪ ሳፕላይ ቢሮ የሚከፈት ሲሆን ሰነዳቸው የተሟላ ከሆነ ባይገኙም የጨረታ ሰነዱ ይከፈታል::

4. አሸናፊ ተጫራቾች ጨረታውን ካሸነፉበት ቀን ጀምሮ በ 4 ቀናት ውስጥ እቃውን መቐለ ዋና መስራቤት ማስረከብ አለባቸው::ይህ ካልሆነ ግን ለጨረታው ማስከበርያ ያስያዙት ብር ለድርጅቱ ገቢ ሆኖ ድርጅቱ ሌላ አማራጭ ይወስዳል::

5. ተጫራቾች ለድርጅታችን አዲስ ከሆኑ ካሁን በፊት ተመሳሳይ እቃ ያቀረቡበት ድርጅት የድጋፍ ደብዳቤ ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው::

6. ተጫራቾች የሚያስገቡት ዋጋ ቫት(VAT) ጨምሮ መሆኑና አለመሆኑን በግልፅ መጠቀስ አለበት:: ይህ ካልሆነ ግን ያስገቡት ዋጋ ቫት እንደሚያካትት ተቆጥሮ ይወሰዳል::

7. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበርያ በባንክ ክፍያ ማዘዣ (ሲፒኦ ) ብር 250,000.00 (ሁለት መቶ ሃምሳ ሺህ ብር) በታሸገ ፖስታ ከጨረታው ጋር ማስገባት አለባቸው በፖስታ ያልታሸገ ሲፒኦ ተቀባይነት የለውም::

8. የእቃው ዝርዝር ከዚህ ጋር የተያያዘ ባለ አንድ ገፅ የግዢ መጠየቅያ ሰነድ ቁጥር 461429 ይመልከቱ::

9. ተጫራቾች በሌላ ተጫራቾች ዋጋ ተመስርተው ዋጋ ማስገባት አይፈቀድም::

10. ተጫራቾች ይህን ጨረታ ካሸነፉ ለሌላ ሶስተኛ ወገን አሳልፎ መስጠት አይችሉም::

11. ተጫራቾች ተጫርተው ያሸነፉት እቃ መቐለ ዋና መስርያ ቤት ድረስ መጥተው ማስረከብ አለባቸው:: ክፍያ በተመለከተ ያቀረቡት እቃ ድርጅታችን ጥራት ቁጥጥር ባለሙያ ተፈትሾ ተቀባይነት ካገኘ በኃላ ክፍያው የሚፈፀም ይሆናል::

12. ኩባንያው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው::

ድሕሪት
ጨረታ መደብ