የመንግስት ሠራተኞች ማኀበራዊ ዋስትና አስተዳደር ማይጨው ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ለቢሮ አገልግሎት የሚውል ቤት ኪራይ በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል
  • የተለቀቀበት ቀን: ሰኞ መስከረም 20, 2017 (ከ 1 ቀን)
  • መዝግያ ቀን: በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀን አየር ላይ ውሎ በ16ኛው ቀን እስከ 11፡00 ሰዓት‍‍‍‍‌‍‌‍‌‌‌‍‍‍‌‍
  • የጨረታ ማስከበርያ ዋጋ:
  • ቦታ: ማይጨዉ
  • የጨረታ ደኩመንት ዋጋ:
  • ጨረታ ሚከፈትበት ቀንና ሰዓት: አልተገለጸም
  • ገዛ/ህንፃ ክራይ/
  • Print
  • Pdf

የግልጽ ጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ ማስታወቂያ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏

የመንግስት ሠራተኞች ማኀበራዊ ዋስትና አስተዳደር ማይጨው ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ለቢሮ አገልግሎት የሚውል ቤት ኪራይ በጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።

በዚሁ መሠረት፡

  1. ቤቱ ሙሉ ግቢ ወይም ህንጻ ሆኖ 14 ከፍሎች ያሉትና (የእያንዳንዱ ክፍል ስፋት ቢያንስ 3 × 4) የሆነ፣ ለደንበኞች አገልግሎት ለመስጠት አመቺና ለዋና መንገድ ቅርብ የሆነ፣
  2. የጽ/ቤቱን ሠራተኞች እና ተገልጋዮች ከሚያውኩ የድምጽ ብክለት የራቀ እንዲሁም አጎራባች ቤቶች እና ህንጻ ውስጥ የቢሮ አገልግሎቱን የሚያውኩ ሁኔታዎች የሌለው፣
  3. የይዞታ ካርታ እና ዓመታዊ ግብር የተከፈለ መሆኑን ማስረጃ የሚያቀርብ፣
  4. የራሱ የሆነ መጸዳጃ ቤትና የጥበቃ ቤት ያለውን
  5. የራሱ የሆነ የኤሌክትሪክ ቆጣሪ፡ የውሃና የስልክ መስመር ያለው፣
  6. ለሚያከራየው ቤት የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ ከሆነ በሚቀርበው ዋጋ ላይ ቫት ስለመካተቱ መግለጽ የሚኖርበት ሲሆን የኪራይ ቆይታ ጊዜው ለ3 ዓመት ውል መግባት ፈቃደኛ የሆነ፡፡
  7. ከላይ የተዘረዘሩትን መስፈርት የምታሟሉ ህጋዊ ተጫራቾች ዝርዝር መግለጫ የያዘውን ሰነድ ከሰሜን ሪጅን ማይጨው ቅ/ጽ/ቤት ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
  8. ጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ው የሚከፈተው ማስታወቂያ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀን አየር ላይ ውሎ በ16ኛው ቀን እስከ 11፡00 ሰዓት‍‍‍‍‌‍‌‍‌‌‌‍‍‍‌‍ ድረስ በሰሜን ሪጅን ማይጨው ቅ/ጽ/ቤት በተዘጋጀው ሳጥን ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነድ መመለስ የሚችሉ መሆኑን እንገልጻለን። ጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ው የሚከፈተው የቀረቡት ፖስታዎች ሳይከፈቱ እንደታሸጉ ወደ ዋናው መ/ቤት ተልከው በአዲስ አበባ ነው። በዚሁ መሠረት ለቢሮ አገልግሎት የሚሆኑ ክፍሎችን ብዛት እና ስፋት በግልጽ በካሬ ሜትር፣ የአንድ ወርና የአንድ ዓመት ከፍያውን በማስላት በተዘጋጀው ሰንጠረዥ ውስጥ መግለጽ አለባቸው፡፡

ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር፡-034 777 0289

የመንግስት ሠራተኞች ማኅበራዊ ዋስትና

አስተዳደር የሰሜን ሪጅን ማይጨው ቅ/ጽ/ቤት

መመለስ
የጨረታ ምድብ