በወረዳ ራያ ኣዘቦ ዕቅድና ፋይናንስ አስተዳደር ፅህፈት ቤት የሚገኝ የግዥና ንብረት አስተዳደር የስራ ሂደት በ2018 ዓ/ም በጀት ኣመት ከ FSR በተገኘ ድጋፍ በዓለም ባንክ ፍቃድ ቁጥር ET-TIGRAY FSRP-514917-CW-REQ በቀበሌ ሃውልቲ ማዕገል መላሕሶ ለማስገንባት ስለ ፈለገ በማንኛውም ደረጃ ፍቃድ የሚገኙ የውሃ ነክ ስራ ተቋራጮች ኣወዳድሮ ለማስገንባት ይፈልጋል።
  • የተለቀቀበት ቀን: ቀዳሜ ኅዳር 20, 2018 ( ከ 3 ወር)
  • መዝግያ ቀን: ኣርብ ኅዳር 26, 2018 09:00 ከሰአት (ተዘጋ)
  • የጨረታ ማስከበርያ ዋጋ: 15000.00
  • ቦታ: ራያ ዓዘቦ
  • የጨረታ ደኩመንት ዋጋ: 200.00
  • ጨረታ ሚከፈትበት ቀንና ሰዓት: ኣርብ ኅዳር 26, 2018 09:30 ከሰአት
  • የቤት/ህንፃ ግንባታ
  • Print
  • Pdf

ፐርፎርማ ማስታወቅያ

በወረዳ ራያ ኣዘቦ ህንፃና ትራንስፖርት አስተዳደር ፅህፈት ቤት የሚገኝ የስራ ሂደት ቁጥጥር ዲዛይንና ህንፃ ስራዎች በ2018 በጀት ኣመት ከ FSRP በተገኘ ድጋፍ የተበጀተ በጀት በቀበሌ ሆረዳ የእንስሳ ማከምያ (Animal Crush) ግንባታ ለማስገንባት ስለ ፈለገ በማንኛውም ደረጃ ፍቃድ የሚገኙ BC/GC ስራ ተቋራጮች ኣወዳድሮ ለማስገንባት ይፈልጋል። በዚህ ጨረታ ለመሳተፍ ከአከባቢ ብክለት ፣ ከሰራተኞች ደህንነት የሚያጓድሉ ተግባራት፣ ከህፃናት ጉልበት ብዝበዛ ፣ ከፆታዊ ትንኮሳና ፆታዊ ጥቃት ነፃ መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡

1) ቴክኒካል ተጫራቾች ጨረታው ላይ ለመሳተፍ ግዴታ ከዚህ በታች የተገለፁ ዝርዝሮች ሟሟላት ኣለባቸው።

1.1) የ2018 ኣ/ም የታደሰ የስራ ተቋራጭ ፍቃድ ፣የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት እና ንግድ ፍቃድ ፣የኮንስትራክሽን የተኮናታሪነት ምዝገባ ካርድ፣ የግብር ከፋይ ሰርተፍኬት/T የቫት ምዝገባ ምስክር ወረቀትና ያለፈው ወር የቫት ዲክለሬሽን ማቅረብ ኣለበት።

1.2) ተጫራቾች ከ2011 ዓ/ም ጀምሮ ባለፉት ሰባት አመታት የሰሩት የሁለት ፕሮጀክት የእያንዳንዱ ፕሮጀክት ቢያንስ 300,000 ብር እና ከዛ በላይ የሰሩ መሆኑን ከኣሰሪው ኣካል የመልካም ስራ አፈፃፀም የፕሮጀክቱ ውል፣ ግዝያዊ ወይም የመጨረሻ ርክክብ ማስረጃ እና የፕሮጀክቱ የመጨረሻ ክፍያ ሰነድ በሚነበብ በኮፒ ማቅረብ አለባቸው።

1.3) ተጫራቾች ግንባታውን ገንብተው ለማስረከብ የተሰጡትን 60 /ስልሳ ቀናት የስራ መርሃ ግብር ወይም የስራ ዕቅድ ማቅረብ ኣለባቸው።

1.4) የጨረታ ማስከበርያ ብር 15,000 /አስራ አምስት ሺ ብር/ ከዚህ ከተዘረዘሩት ባኣንዱ የሚቀርብ ሁኖ በኢትዮጽያ በሄራዊ ባንክ ከተፈቀደላቻው ባንኮች የሚሰጥ በሁኔታዎች ያላተመሰረተ ዋስትና ከባንኮች ወይም ሲፒኦ (CPO) ወይም ፋይናንሳዊ ድርጅቶች ባረጋገጠው ቼክ ሌተር ኦፍ ክሬዲት ማቅረብ ኣለባቸው።

1.5) ኣሸናፊው ተጫራች ወይም የስራ ተቋራጭ : ሳይት ከተረከበበት ቀን ጀምሮ አግባብነት ያላቸው የከባቢ ጥበቃ እና የዓለም ባንክ የአከባቢ ፣ ማህበራዊ ፣ ማህበረ ሰብ ና የፕሮጀክቱ ሰራተኞች ጤናና ደሕንነት የተመለከቱ ሕጎች ፣ ስታንዳርዶች ፣ የምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም የአከባቢና ማሕበራዊ ደህንነት አያያዝና አስተዳድር ማእቀፎች የማክበርና በስራው ምክንያት ሊደርስ የሚችል ጉዳት ኣስቀድሞ የመከላከል እና ጉዳቱ ከደረሰም በራሱ ወጭ ጉዳቱን የማስተካከል ወይ ማከም ግዴታ ኣለበት ። እንዲሁም ስራው ጨርሶ ከመውጣቱ በፊት ለጎርፍ ፣ የእንስሳትና ሰው ጤንነት እና ደህንነት፣ ለአደጋ የሚያጋልጡ ነገሮች ሁሉ አስተካክሎ ወይም ኣስወግዶ የመውጣት ግዴታ ኣለበት ። ይህን ለማስፈፀም የሚያስችለው የአከባቢና ማሕበራው ደህንነትና ጤንነት አያያዝና አስተዳደር ስተራቴጀክ ዕቅድና ኮድ ኦፍ ኮንዳክት ማቅረብ ይጠበቅበታል

2) ተጫራቾች ግንባታውን ሳይት ከተረከቡበት ቀን ጀምሮ በ 60 /ስልሳ ተከታታይ ቀናቶች ሙሉ በሙሉ ጨርሰው ማስረከብ ኣለባቸው።

3) ተጫራቾች በህንፃና ትራንስፖርት አስተዳደር ወረዳ ራያ ኣዘቦ የሚገኝ የስራ ሂደት ቁጥጥር ዲዛይንና ህንፃ ስራዎች የተዘጋጀ የጨረታ ሰነድ ከቀን 19/03/2018 ኣ/ም ጀምሮ ከራያ ዓዘቦ ህንፃና ትራንስፖርት አስተዳደር የሚገኝ የስራ ሂደት ቁጥጥር ዲዛይንና ህንፃ ስራዎች መውሰድ ይችላሉ ።

4) ተጫራቾች የተጠየቁትን የቴክኒካል መሰፈርት በሶስት (3) ኮፒ በተለያየ ፖስታ በማሸግ ደግመው ሶስቱ የታሸጉትን የቴክኒካል መሰፈርት በአንድላይ በሌላ ትልቅ ፖስታ በማሸግ ከላዩላይ ቴክኒካል ሰነድ ተብሎ በሚታይ ቀለም በመፃፍ ማቅረብ አለባቸው ።

5) ተጫራቾች ፋይናንሻል ሰነዶች ኣንድ ኦርጅናል ፣ ሁለት ፎቶ ኮፒ በተለያዩ ፖስታ ካሸጉ ብሃላ ኦርጅናልና ኮፒ በማለት ከላዩላይ በሚታይ ቀለም በመፃፍ በአንድላይ በሌላ ትልቅ ፖስታ በማሸግ ከላዩላይ ፋይናንሻል ሰነድ ተብሎ ብሚታይ ቀለም መፃፍ አለባቸው ።

6) ተጫራቾች በተለያየ ፖስታ የታሸገውን ቴክኒካልና ፋይናንሻል ሰነዶች ባንድ ላይ በሌላ ትልቅ ፖስታ ከሸጉ ብሃላ የሚጫረቱበትን የፕሮጀክት ሙሉ አድራሻና የተጫራች ሙሉ ስም ከትሉቁ ፓስታ ላይ ብሚታይ ቀለም በመፃፍ ለጨረታው ተብሎ ከተዘጋጀው ከቢሮ ቁጥር 28 ከተዘጋጀው ሳጥን እስከ 26/03/2018 ኣ/ም ከጥዋቱ 3:00 ሰኣት በኣካል በመምጣት ማስገባት ኣለባቸው ።

7) ተጫራቾች ጨረታውን በትኩረት ተረድተው ዋጋ ከሞሉ ብሃላ ፊርማቸው እና ማህተማቸው በየአንዳንዱ ገፅ

በማሳረፍ እንደ ተሽጦ የነበረው ሰነድ ሳያጎድሉ ማቅረብ ኣለባቸው።

8) ተጫራቾች ያስገቡትን ሰነድ ስርዝ ካለበት እና ካልተፈረመበት እንዲሁም የነጥብና የብር መለያ ለመለየት አሻሚ (አዳጋች) ከሆነ ቀጥታ ከጨረታ ውጪ ይሆናሉ ።

9) ጨረታው ሁሉም ተጫራቾች በተገኙበት ወይ ደግሞ ህጋዊ ወኪሎ በተገኘበት በቀን 26/03/2018 ኣ.ም ከጥዋቱ 9:00 ታሽጎ ልክ 9:30 በህንፃና ትራንስፖርት አስተዳደር ወረዳ ራያ ኣዘቦ የሚገኝ የስራ ሂደት ቁጥጥር፣ ዲዛይንና ህንፃ ስራዎች ቢሮ ቁጥር 28 ጨረታው ይከፈታል።

10) ተጫራቾች አሸናፊ መሆናቸው ሲረጋገጥ የውል ማስከበሪያ ከኢትዮጽያ በሄራዊ ባንክ ወይም በኢትዮጽያ በሄራዊ ባንክ ከተፈቀደላቻው ባንኮች የሚሰጥ በሁኔታዎች ያልተመሰረተ ዋስትና ወይም ሲፒኦ (CPO) 10% ማስያዝ ይኖርባቸዋል።

11) ተጫራቾች አሸናፊ መሆናቸው ሲረጋገጥ ቅደመ ክፍያ የሚጠይቁ ከሆነ ከኢትዮጽያ በሄራዊ ባንክ ወይም በኢትዮጽያ በሄራዊ ባንክ ከተፈቀደላቻው ባንኮች የሚሰጥ በሁኔታዎች ያልተመሰረተ ዋስትና ሲፒኦ (CPO)

የውሉ 20% በማስያዝ የሚሰጣቸው ይሆናል ።

11) ተጫራቾች አሸናፊ መሆናቸው ሲረጋገጥ ቅደመ ክፍያ የሚጠይቁ ከሆነ ከኢትዮጽያ በሄራዊ ባንክ ወይም

በኢትዮጽያ በሄራዊ ባንክ ከተፈቀደላቻው ባንኮች የሚሰጥ በሁኔታዎች ያልተመሰረተ ዋስትና ሲፒኦ (CPO) የውሉ 20% በማስያዝ የሚሰጣቸው ይሆናል ።

12) ጨረታው ኣሸናፊ የሚሆነው ቴክኒካል ሙሉ ያለፈ ወደ ፋይናሻል ውድድር ገብቶ ዝቅተኛ ዋጋ ያስገባ

ይሆናል ። ቴክኒካል ሙሉ ያላሞላ ለፋይናንሻል ውድድር አይቀርብም ።

13) የጨረታ ሰነድ በስራ ስአት በህንፃና ትራንስፖርት አስተዳደር ወረዳ ራያ ኣዘቦ የሚገኝ የስራ ሂደት ቁጥጥር ዲዛይንና ህንፃ ስራዎች ቢሮ ቁጥር 28 መጥተው መውሰድ ይችላሉ ።

14) ፅህፈት ቤቱ የተሻለ ኣማራጭ ከገኘ ጨረታው በሙሉ ወይ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። 15) የተሻለ መረጃ ለማግኘት በህንፃና ትራንስፖርት አስተዳደር ወረዳ ራያ ኣዘቦ የሚገኝ የስራ ሂደት ቁጥጥር፣ ዲዛይንና ህንፃ ስራዎች ቢሮ ቁጥር 28 ብኣካል በመቅረብ ወይ ደግሞ በስልክ ቁጥር 034-66-40-181 (0910338850) በመደወል ማግኘት ይችላሉ።

መመለስ
የጨረታ ምድብ
  • ሶፍትዌርና ኔትዎርክ (26)
    • ኮንስትራክሽን (301)
      • ኤሌትክትሮኒክስና ኣይሲቲ እቃዎች (553)
        • የሂሳብ ኣያያዝና ኦዲት ማድረግ (74)
          • ግብርና (198)
            • የግንባታ እቃዎች (1266)
              • ፅዳትና የንፅህና እቃዎች (234)
                • ማማከር (41)
                  • ትምህርትና ስልጠና (27)
                    • ኤሌክትሪካልና ኤሌክትሮ መካኒካል (393)
                      • ምግብና መጠጥ (175)
                        • እግድ (56)
                          • ፈርኒሽንግና ፊክስቸር (19)
                            • ፈርኒቸር (230)
                              • ጠቅላላ ስራዎች አገልግሎት (27)
                                • ስጦታዎች እና እደ-ጥበብ (2)
                                  • ጤና (41)
                                    • የቤት ዕቃዎች (44)
                                      • ኢንሹራንስ (1)
                                        • የላብራቶሪ እቃዎች እና ኬሚካል (182)
                                          • መሬትና ሊዝ (3)
                                            • ጥገና (81)
                                              • የህክምና ዕቃዎች (63)
                                                • መኣድና የተፈጥሮ ሃብት (4)
                                                  • የቢሮ እቃዎችና የፅህፈት መሳሪያዎች (268)
                                                    • ማሸግያ መጠቅለያ እና ወረቀቶች (3)
                                                      • ፎቶግራፍና ፊልም (6)
                                                        • የህትመት ስራዎች (110)
                                                          • የማስታወቅያ ስራዎች (11)
                                                            • ኪራይ (213)
                                                              • ሽያጭ (333)
                                                                • የጥበቃ ስራዎችና ሰኪዩሪቲ (40)
                                                                  • የተሽከርካሪ መለዋወጫ እቃዎች (627)
                                                                    • የስፖርትና ትጥቅና ተዛማጅ እቃዎች (44)
                                                                      • ቴሌኮምኒኬሽን እቃዎች (13)
                                                                        • ጨርቃ ጨርቅና የቆዳ ውጤቶች (286)
                                                                          • የትራንዚትና መጓጓዠያ ኣገልግሎት (100)
                                                                            • የተሽከርካሪና ከባደ ማሽነሪ (166)
                                                                              • መጋዝን (25)
                                                                                • እንጨት እና የእንጨት ስራ (76)
                                                                                  • ኣልሙኒየም፡ መስትዋትና የብረታ ብረት ስራዎች (88)
                                                                                    s