የግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ
ኩባንያችን መስፍን ብረታ ብረት ና ኢንጂነሪንግ ኃላ.የተወ የግል ኩባንያ (FSWE ኢንድስትሪ) ከታች በሰንጠረዡ የተፃፈው የተለያዪ መጠን ያላቸው Sanitary Materials & Stationary & Prirting Materials በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ስለሚፈልግ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተወዳዳሪዎች እንድትሳተፉ ኩባንያችን ይጋብዛል::
| ተ.ቁ | የዕቃው ዓይነት ዝርዝር | መለኪያ | ብዛት | ማብራርያ |
|---|---|---|---|---|
| 01 | Powder Detergent | pieces | 2,000 | 100 grm |
| 02 | Soap | pieces | 1,000 | 200 grm |
| 03 | Soap for Body | pieces | 1,000 | 70 gri |
| 04 | Paper, Computer A4 size | pieces | 500 | 80 grm |
| 05 | Pen,Blue | pieces | 1,000 |
የጨረታው መስፈርት
1. ተጫራቾች በዘርፉ የ2017 ዓ/ም የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር እና የሰኔ ወር ቫት ማሳወቅያ ሰነድ ፎቶ ኮፒ በማያያዝ ከጨረታው ዝርዝር (ሰነድ) ጋር ማስገባት ይኖርባቸዋል::
2. ተጫራቾች የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር እና የሰኔ ወር ቫት “ማሳወቅያ ሰነድ ፎቶ ኮፒ የማይመለስ እና ኦርጅናል የሚመለስ በመያዝ የጨረታ ሰነድ ክቀን ከ 24/08/2025 እ.ኤ.አ ጀምሮ እስከ 08/09/2025 እ.ኤ.አ መቐለ ላጪ ቅርንጫፍ FSWE ኢንድስትሪ በስራ ሰኣት መውሰድ ይኖርባቸዋል::
3. ጨረታው 08/09/2025 እ.ኤ.አ ከቀኑ 4:00 ተዘግቶ በተመሳሳይ ቀን ከሰኣት 4:15 ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው በተገኙበት መቐለ ዋና መስርያ ቤት በሚገኝ ላጪ FSWEI ኢንድስትሪ ሳፕሳይ ቢሮ የሚከፈት ሲሆን ሰነዳቸው የተሟላ ከሆነ ባይገኙም የጨረታ ሰነዱ ይከፈታል::
4. አዲስ አበባ ለሚገኙ ተጫራቾች መቐለ ላጪ መስርያ ቤት በሚገኝ FSWE ኢንድስትሪ ሳፕላይ ቢሮ የጨረታ ሳንዱቅ ማስገባት ይኖርባቸዋል:
5. ተጫራቾች የሚያስገቡት ዋጋ ቫት(VAT) ጨምሮ መሆኑና አለመሆኑን በግልፅ መጠቀስ አለበት:: ይህ ካልሆነ ግን ያስገቡት ዋጋ ቫት እንደሚያካትት ተቆጥሮ ይወሰዳል::
6. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበርያ በባንክ ክፍያ ማዘዣ (ሲፒኦ ) ብር 10,000.00 (ኣስር ሺህ ብር) ለፅዳት እቃዎች እንዲሁም ሰስተሽነሪ እቃዎች ብር ብር 15,000.00 (ኣስራ ኣምስት ሺህ ብር) በታሸገ ፖስታ ከጨረታው ጋር ማስገባት አለባቸው::በፖስታ ያልታሸገ ሲፒኦ ተቀባይነት የለውም፡፡
7. አሸናፊ ተጫራቾች ጨረታውን ማሸነፋቸው የግዥ ማዘዣ ከደረሳቸው ቀን ጀምሮ ያቀረቡትን ናሙና ተቀባይነት ካገኘ በ 5 ቀናት ውስጥ የጠቅላላ ዋጋ ቫት ጨምሮ 10% የውል ማስከበርያ የባንክ ዋስትና (Unconditional bank guarantee) በማሰራት ከኩባንያችን ጋር ውል መፈራረም አለባቸው:: ይህ ካልሆነ ግን ለጨረታ ማስከበርያ ያስያዙት ብር ለድርጅቱ ገቢ ሆኖ ድርጅቱ ሌላ አማራጭ ይወስዳል::
8. አሸናፊ ተጫራቾች ጨረታውን አሸንፈው ውል ካሰሩበት ቀን ጀምሮ በ
ተከታታይ ቀናት ውስጥ እቃው ማስረከብ አለባቸው::ይህ ካልሆነ ግን ለውል ማስከበርያ ያስያዙት ብር ለድርጅቱ ገቢ ሆኖ ድርጅቱ ሌላ አማራጭ ይወስዳል::
9. ተጫራቾች በሌላ ተጫራቾች ዋጋ ተመስርተው ዋጋ ማስገባት አይፈቀድም::
10. ተጫራቾች ይህን ጨረታ ካሸነፉ ለሌላ ሶስተኛ ወገን አሳልፎ መስጠት አይችሉም::
11. ተጫራቾች ተጫርተው ያሸነፉት እቃ መቐለ ዋና መስርያ ቤት ድረስ መጥተው ማስረከብ አለባቸው:: ክፍያ በተመለከተ ያቀረቡት እቃ ድርጅታችን ጥራት ቁጥጥር ባለሙያ ተፈትሾ ተቀባይነት ካገኘ በኃላ የሚፈፀም ይሆናል::
12. ኩባንያው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ
ነው::
| ለበለጠ መረጃ | |
|---|---|
| መቐለ | አዲስ-አበባ |
| ስልክ-+251914729699 | ስልክ-+251-914726541 |
| ፋክስ-+251-344406225 | ፋክስ-+251-114709636 |