Mesfin Industrial Engineering PLC

የግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ

ኩባንያችን መስፍን ብረታ ብረት ና ኢንጂነሪንግ ኃላ.የተወ የግል ኩባንያ (FSWE ኢንድስትሪ) ከታች በሰንጠረዡ የተፃፈው የተለያዪ መጠን ያላቸው Sanitary Materials & Stationary & Prirting Materials በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ስለሚፈልግ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተወዳዳሪዎች እንድትሳተፉ ኩባንያችን ይጋብዛል::

ተ.ቁየዕቃው ዓይነት ዝርዝርመለኪያብዛትማብራርያ
01Powder Detergentpieces2,000100 grm
02Soappieces1,000200 grm
03Soap for Bodypieces1,00070 gri
04Paper, Computer A4 sizepieces50080 grm
05Pen,Bluepieces1,000

የጨረታው መስፈርት

1. ተጫራቾች በዘርፉ የ2017 ዓ/ም የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር እና የሰኔ ወር ቫት ማሳወቅያ ሰነድ ፎቶ ኮፒ በማያያዝ ከጨረታው ዝርዝር (ሰነድ) ጋር ማስገባት ይኖርባቸዋል::

2. ተጫራቾች የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር እና የሰኔ ወር ቫት “ማሳወቅያ ሰነድ ፎቶ ኮፒ የማይመለስ እና ኦርጅናል የሚመለስ በመያዝ የጨረታ ሰነድ ክቀን ከ 24/08/2025 እ.ኤ.አ ጀምሮ እስከ 08/09/2025 እ.ኤ.አ መቐለ ላጪ ቅርንጫፍ FSWE ኢንድስትሪ በስራ ሰኣት መውሰድ ይኖርባቸዋል::

3. ጨረታው 08/09/2025 እ.ኤ.አ ከቀኑ 4:00 ተዘግቶ በተመሳሳይ ቀን ከሰኣት 4:15 ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው በተገኙበት መቐለ ዋና መስርያ ቤት በሚገኝ ላጪ FSWEI ኢንድስትሪ ሳፕሳይ ቢሮ የሚከፈት ሲሆን ሰነዳቸው የተሟላ ከሆነ ባይገኙም የጨረታ ሰነዱ ይከፈታል::

4. አዲስ አበባ ለሚገኙ ተጫራቾች መቐለ ላጪ መስርያ ቤት በሚገኝ FSWE ኢንድስትሪ ሳፕላይ ቢሮ የጨረታ ሳንዱቅ ማስገባት ይኖርባቸዋል:

5. ተጫራቾች የሚያስገቡት ዋጋ ቫት(VAT) ጨምሮ መሆኑና አለመሆኑን በግልፅ መጠቀስ አለበት:: ይህ ካልሆነ ግን ያስገቡት ዋጋ ቫት እንደሚያካትት ተቆጥሮ ይወሰዳል::

6. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበርያ በባንክ ክፍያ ማዘዣ (ሲፒኦ ) ብር 10,000.00 (ኣስር ሺህ ብር) ለፅዳት እቃዎች እንዲሁም ሰስተሽነሪ እቃዎች ብር ብር 15,000.00 (ኣስራ ኣምስት ሺህ ብር) በታሸገ ፖስታ ከጨረታው ጋር ማስገባት አለባቸው::በፖስታ ያልታሸገ ሲፒኦ ተቀባይነት የለውም፡፡

7. አሸናፊ ተጫራቾች ጨረታውን ማሸነፋቸው የግዥ ማዘዣ ከደረሳቸው ቀን ጀምሮ ያቀረቡትን ናሙና ተቀባይነት ካገኘ በ 5 ቀናት ውስጥ የጠቅላላ ዋጋ ቫት ጨምሮ 10% የውል ማስከበርያ የባንክ ዋስትና (Unconditional bank guarantee) በማሰራት ከኩባንያችን ጋር ውል መፈራረም አለባቸው:: ይህ ካልሆነ ግን ለጨረታ ማስከበርያ ያስያዙት ብር ለድርጅቱ ገቢ ሆኖ ድርጅቱ ሌላ አማራጭ ይወስዳል::

8. አሸናፊ ተጫራቾች ጨረታውን አሸንፈው ውል ካሰሩበት ቀን ጀምሮ በ

ተከታታይ ቀናት ውስጥ እቃው ማስረከብ አለባቸው::ይህ ካልሆነ ግን ለውል ማስከበርያ ያስያዙት ብር ለድርጅቱ ገቢ ሆኖ ድርጅቱ ሌላ አማራጭ ይወስዳል::

9. ተጫራቾች በሌላ ተጫራቾች ዋጋ ተመስርተው ዋጋ ማስገባት አይፈቀድም::

10. ተጫራቾች ይህን ጨረታ ካሸነፉ ለሌላ ሶስተኛ ወገን አሳልፎ መስጠት አይችሉም::

11. ተጫራቾች ተጫርተው ያሸነፉት እቃ መቐለ ዋና መስርያ ቤት ድረስ መጥተው ማስረከብ አለባቸው:: ክፍያ በተመለከተ ያቀረቡት እቃ ድርጅታችን ጥራት ቁጥጥር ባለሙያ ተፈትሾ ተቀባይነት ካገኘ በኃላ የሚፈፀም ይሆናል::

12. ኩባንያው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ

ነው::

ለበለጠ መረጃ
መቐለአዲስ-አበባ
ስልክ-+251914729699ስልክ-+251-914726541
ፋክስ-+251-344406225ፋክስ-+251-114709636