ባንኪ ልማት ኢትዮጵያ

የሐራጅ‍‍‍‍‌‍‌‍‌‌‌‍‍‍‌‍ ማስታወቂያ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ መቐለ ዲስትሪክት የገነት ጠብታ አግሮ ፕሮሰሲንግ ኃላ/የተ/የግ/ማህበር ለሰጠው ብድር አመላለስ በዋስትና የያዘውንና ከዚህ በታች ባለው ሰንጠረዥ የተመለከተውን ንብረት በአዋጅ ቁጥር 97/90፤ 216/92 እና 1147/11 በተሰጠው ስልጣን መሠረት በሐራጅ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡

የተበዳሪው/ መያዣ ሰጪው ሰም

ለሐራጅ የቀረበ ንብረት ዓይነትና ዝርዝር

የቦታው ስፋት በካ/ሜ

ንብረቱ የሚገኝበት አድራሻ

የሐራጁ መነሻ ዋጋ/ብር/

የሐራጁ ደረጃ

ሐራጅ የሚካሄድበት ቀን እና ሰዓት‍‍‍‍‌‍‌‍‌‌‌‍‍‍‌‍

ዞን

ከተማ

ቀበሌ

የገነት ጠብታ አግሮ ፕሮሰሲንግ ኃላ/የተ/የግ/ማህበር

የቲማቲም ማቀናበርያ ፋብሪካ ህንፃ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ቁጥር 2969/2005 የሆነ ማሽነሪዎች እና አይስዙ

3,500ካ/ሜ

ትግራይ

አድዋ

ደብርቺ

10,558,627.77 /አስር ሚሊዮን አምስት መቶ ሃምሳ ስምንት ሺህ ስድስት መቶ ሃያ ሰባት ብር ከ77 ሳንቲም/

ሁለተኛ

ነሃሴ 07 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 4:00-6:00 ሰዓት

ማሳሰቢያ፡-

  1. ተጫራቾች ንብረቱን ለመጎብኘት ከፈለጉ አሰቀድሞ ከባንኩ ጋር ቀጠሮ በመያዝ ከሐራጁ ቀን በፊት ንብረቱን መጎብኘት ይችላሉ፡፡
  2. ተጫራቾች የሐራጁን መነሻ ዋጋ 25% (ሃያ አምስት በመቶ) በባንከ ማዘዣ ሲፒኦ (CPO) ብቻ አሰርተው ከሐራጁ ቀን በፊት ማስያዝ ወይም ሐራጁ በሚካሄድበት ዕለት ሐራጁ ከመከፈቱ በፊት ይዘው መቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ በሐራጁ የተሸነፉ ተጫራቾች ያስያዙት ሲፒኦ (CPO) ወዲያውኑ ይመለስላቸዋል፡፡
  3. በሐራጁ ለመሳተፍ የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች ሐራጁ ከመጀመሩ በፊት ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት በፊት ባለው ጊዜ ሐራጁ በሚካሄድበት ቦታ በአካል ወይም ሕጋዊ ወኪል በኩል ቀርቦ መመዝገብ ይኖርበታል፡፡
  4. ሐራጁ ከላይ በተገለፀው ቀንና ሰዓት ተበዳሪው/ መያዣ ሰጪው ወይም ህጋዊ ወኪላቸው፣ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸውና ታዛቢዎች በተገኙበት በፕሮጀክቱ ቅጥር ግቢ ውስጥ ይካሄዳል፡፡ በጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ ቀንና ሰዓት መያዣ ሰጪው ወይም ህጋዊ ወኪላቸው እና ታዛቢዎች ባይገኙም ሐራጁ ይካሄዳል፡፡
  5. በሐራጁ የተሻለ ዋጋ ያቀረበ ተጫራች ማሸነፉን የሚገልፅ ደብዳቤ ከባንኩ ሲደርሰው አሸናፊ ይሆናል፡፡
  6. ሐራጁን ያሸነፈ ተጫራች አሸናፊ መሆኑ በፅሁፍ ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ ያሸነፈበትን ዋና በ15ተከታታይ ቀናት ጊዜ ውስጥ ለባንኩ አጠቃሎ ገቢ ማድረግ ይኖርበታል፡፡ በተገለፀው ጊዜ ውስጥ አሸናፊው ገንዘቡን ገቢ ካላደረገ ሐራጁ ይሰረዛል፤ ያስያዘው ገንዘብም ለባንኩ ገቢ ይሆናል፡፡ ሐራጁን ያሸነፈ ተጫራች ያሸነፈበትን ገንዘብ በጥሬ ለባንኩ መክፈል ይኖርበታል፡፡ ሆኖም አሸናፊው በባንኩ የብድር ፖሊሲ መሠረት አስፈላጊውን መስፈርቶች ካሟላና የፕሮጀክቱን ስራ የሚያስቀጥል ከሆነ ንብረቱን በከፊል ብድር ለመግዛት መጠየቅ ይችላል፡፡
  7. የጉምሩክ ቀረጥና ታክስ ያልተከፈለባቸው ተሽከርካሪ እና ማሽነሪዎች በተመለከተ ገዢው የቀረጥ ነፃ መብት ሊኖረው ይገባል ወይም በንብረቶቹ ላይ በመንግስት የሚፈለገውን ቀረጥና ታክስ መክፈል ይኖርበታል፡፡
  8. ንብረቱ ስሙ ንብረት ለገዢው እንዲዞር ባንኩ ለሚመለከተው መንግስታዊ አካል ደብዳቤ ይፅፋል፡፡ ገዢው ጉዳዩን ተከታትሎ ያስፈፅማል፡፡
  9. ሐራጁ ከመካሄዱ በፊትም ሆነ ከተካሄደ በኋላ ባንኩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ወይም ብድሩ ከተከፈለ ሐራጁን የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  10. ሐራጁን ያሸነፈ ተጫራች የሽያጩን 15% ተጨማሪ እሴት ታክስ እና ሌሎች ገዥ እንዲከፍላቸው በሕግ የተወሰኑ ክፍያዎች፤ የስም ማዛወሪያ ክፍያን ጨምሮ ይከፍላል፡፡
  11. ለተጨማሪ መረጃ መቐለ ዲስትሪክት ሎን ዎርክአውት ዲቪዥን በአካል በመቅረብ ወይም በስልክ ቁጥር 034-4-40-74-39/ 034-4-41-90-16 ማግኘት ይችላሉ፡፡