ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
በመንግስት ሰራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር ሰሜን ሪጅን የአክሱም ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ለቢሮ አገልግሎት የሚውል ህንፃ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመከራየት ይፈልጋል።
በመሆኑም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ትችላላችሁ፡፡
- ከ13 እስከ 20 ክፍል እና ከ 250 ካሬ ሜትር በላይ ሆኖ ለቢሮ አቀማመጥ እና አገልግሎት አሰጣጥ ምቹ የሆነ
- የእያንዳንዱ ክፍል ስፋት ቢያንስ 3×4m2 እና ከዚያ በላይ የሆነ
- ቤቱ ሽንት ቤት፣ ውሃ፣ ሻውር እና መብራት ኖሮት ከG+1 ያልበለጠ ሲሆን በአክሱም ከተማ ይህንን ማሟላት የሚችሉ የቤት ባለቤቶች መሳተፍ ይችላሉ።
- ከያሬድ ዜማ ሆቴል እስከ ብራና ሆቴል ባለው መስመር ዋናው የአስፋልት መንገድ ግራና ቀኝ እስከ 200 ሜትር ገባ ብሎ
- ተወዳዳሪዎች የተጨማሪ እሴት ታክሰ /ቫት/ እና ቲኦቲ ተመዝጋቢዎች ከሆኑ የማስረጃውን ኮፒ ማቅረብ ያለባቸው ሲሆን የሚሰጡትም ዋጋ ቫት እና ቲኦቲ ያካተተ ወይም ያላካተተ መሆኑን መግለፅ አለባቸው፤ ካልተገለፀ ከነቫት እንደሆነ ተደርጎ ይወሰዳል።
- ተወዳዳሪዎች ቤቱ ህጋዊ ስለመሆኑና የዘመኑን ግብር የከፈለበት ህጋዊ ደረሰኝ ማቅረብ ይኖርባችዋል እንዲሁም የይዞታ ባለቤትነት ማረጋገጫ ኮፒ ማቅረብ ይኖርባችዋል።
- ተጫራቾች ለዚህ ጨረታ የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ የማይመለስ 100 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ የስራ ቀናት ከጠዋቱ 2:00 እስከ 11:00 ድረስ ከሰሜን ሪጅን የአክሱም ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ቀርበው በመግዛት የሚያከራዩበትን የአንድ ወር ዋጋ በመሙላትና በታሸገ ፖስታ ውስጥ በማድረግ ለዚህ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡
- ጨረታው የሚከፈተው ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ በወጣበ16ኛው የስራ ቀን ከቀኑ 8:00 ተዘግቶ በዚያው ቀን 8:30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በዋና መስሪያ ቤት ይከፈታል።
- ጽ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- አድራሻ፦ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሳያዊ ሪፐብሊክ በመንግስት ሰራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር ሰሜን ሪጅን የአክሱም ቅርንጫፍ ጽ/ቤት
- ስልክ ቁጥር፦ 034 775 3366
መመለስ