The Development Bank of Ethiopia

የመጋዘን ኪራይ የጨረታ

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ መቐለ ዲስትሪክት ማሽነሪዎች ለማስቀመጥ የሚያገለግል መጋዘን በጨረታ አወዳድሮ ለአንድ ዓመት (እንደ አስፈላጊነቱ መራዘም የሚችል) ለመከራየት ይፈልጋል። ስለሆነም በጨረታዉ መወዳደር የምትፈልጉ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተመለከቱትን መስፈርቶች በሟሟላት መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልጻ

1. አጠቃላይ የመሬት ይዞታው ከ 2,000 ሜካ ያላነሰ ሆኖ የሼዱ ይዞታ ከ 500 ሜካ ያላነሰ መሆን ይኖርበታል፤

2. የአጥሩ መሰረት በሰሜንት አርማትራ (Grade beam) የተሰራ ቁመቱ ቢያንስ 2.5 ሜትር የሆነ፤

3. የሼዱ ወለል ቢያንስ በሰሜንት አርማርታ የተሞላ፤

4. የሼዱ በር ቁመትና ጎን ቢያንስ 44 ሜትር የሆነ፤

5. የኤሌክትሪክ መብራት ያለው፤

6. የእሳት አደጋ መከላከያ መሳርያዎች ያለው፤

7. ቢያንስ አንደኛ ደረጃ የጠጠር መንገድ ያለው፤

8. የዓመቱ በዘርፉ (በኪራይ እና አከራይ) ህጋዊና የታደሰ የንግድ ፈቃድ፤ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ማስረጃዎች ማቅረብ የሚችሉ፤ የተጨ የሆኑ ፤· እሴት ታክስ /ቫት/ ወይም ቲኦቲ ተመዝጋቢ

9. የመሬት ይዞታ ካርታ(Title dead) እና የሊዝ ውል ኮፒ ማቅረብ የሚችል እንዲሁም ቦታው ለመጋዘን ዐላማ (and Use Purpose for Store or ware house) ብቻ የተሰጠ መሆን ይኖርበታል፤

10. ቅድሚያ ክፍያ በተመለከተ በግልፅ መቀመጥ ይኖርበታል።

11. በጨረታ ሰነዱ ላይ የተሰረዘ ወይም የተደለዘ ሆኖ ለመለየት የሚያስቸግር ከሆነ ተቀባይነት የለዉም።

12. ተጫራቾች የማይመለስ ብር 100 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ በመግዛት ስም እና አድራሻቸውን በመጥቀስ ሌሎች አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎችን በማያያዝ በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ በማድረግ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ መቐለ ዲስትሪክት ምድር ቤት ላይ ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን እስከ የካቲት 9 ቀን 2018 ዓ/ም ከቀኑ 08:00 ድረስ ብቻ ማስገባት የሚቻል ሆኖ ጨረታው በተመሳሳይ ቀን እና ሰዐት ተጨራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የሚከፈት ይሆናል።

13. ዲስትሪክቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ።

ስልክ ቁጥር 0344410233