ኣብ ትካል ሃይሊ መብህቲ ኢትዮ ጨንፈር ሰሜን

የጨረታ ማስታወቂያ

የጨረታ ቁጥር MKREU-001/2018

የመቐለ ሪጅን ኤሌክትሪክ አገልግሎት ለትራንስፎርመር የሚውሉ የተለያዩ ዓይነትና መጠን ያላቸው ኬብል ላግ ዲስትሪቢውሽን ዕቃዎችን በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።

ዝርዝሩም እንደሚከተለው ይሆናል፡-

ሎት

የዕቃው ዓይነትና መጠን

ብዛት

ሎት 1

የተለያየ መጠን ያላቸው ኬብል ላግ/ኩፐር እና አልሚኒየም ለኩፐር /Copper to Copper cable lug & Aluminum to Copper cable lug.

15,300

  1. ማንኛውም በዘርፉ የተሰማራ የታደሰ ንግድ ስራ ፈቃድ ያለው፣ የዘመኑን ግብር የከፈለበትን የታደሰ የንግድ ፈቃድ፤ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምስክር ወረቀት፤ የገንዘብ ሚኒስቴር የምዝገባ የምስክር ወረቀት እና የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር፣ ማስረጃ ያለው መሆን አለበት፤
  2. በጨረታው መሳተፍ ያለባቸው ተጫራቾች በዘርፉ የአቅራቢነት ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፣ መልካም የስራ አፈጻጸም ያላቸው እና ለዚሁ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፤
  3. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ማስታወቂያው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የማይመለስ ብር 1,000.00 (አንድ ሺህ ብር) በመክፈል መውሰድ ይችላሉ፣
  4. አድራሻ፡- መቐለ ከተማ ከፕላኔት ሆቴል ወረድ ብሎ ዛምራ ኮንስትራክሽን ህንፃ ላይ የሚገኘው የመቐለ ሪጅን ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጽ/ቤት 3ኛ ፎቅ ሰፕላይ ቼይን ንብረትና ጠቅላላ አገልግሎት ቢሮ ቁጥር 304፣
  5. ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ የሚያቀርቡት “ለመቐለ ሪጅን ኤሌክትሪክ አገልግሎት" (MEKELLE REGION ELECTRIC UTILITY) ተከፋይ የሆነ የገንዘብ መጠኑ ብር 200,000.00 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) በታወቀ ባንከ የተረጋገጠ ቼክ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንከ ጋራንቲ መሆን ይኖርበታል።
  6. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ኦሪጅናል እና ኮፒ በማለት በተለያየ ፖስታ በማሸግ በአንድ ፖስታ በማድረግ የጨረታ ስቁጥሩ MKREU-001/2018 የሚል ምልክት በማድረግ እስከ ሐምሌ 30/2017 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30 ሰዓትድረስ ከላይ በተጠቀሰው አድራሻ ቢሮ ቁጥር 304 ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፣
  7. ጨረታው ከላይ በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት ተዘግቶ በተመሳሳይ ቀን ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከቀኑ 9፡00 ሰዓት ላይ ይከፈታል፣
  8. ተቋሙ የተሻለ አማራጭ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
  9. ተጫራቾች ተጨማሪ መረጃ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር +251342406712 መደወል ይችላሉ።

የመቐለ ሪጅን ኤሌክትሪክ አገልግሎት