ሚኒስቴር እቶት ኢትዮጵያ ቤት ፅሕፈት መቐለ

ለሁለተኛ ጊዜ የወጣ የሃራጅ ጨረታ ማስታወቅያ--ቁጥር 2/2017

በሽራሮ ጉምሩክ መቆጣጠሪያ ጣቢያ በተለያዩ ጊዚያት ተይዘውና ተወርሰው በአዲነብሪ ኢድ የውርስ መጋዝን የሚገኙ እቃዎች ማለትም ምግብ ነክ እቃዎች ፤ አልባሳትና ጫማዎች ፤ የቢሮና የቤት እቃዎች ባሉበት ቦታና ሁኔታ ብሓራጅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሽጥ ይፈልጋል፡፡

1. በመሆኑ ቅ/ፅ/ቤቱ ባወጣው የዕቃ ሽያጭ ጨረታ ወዳደር የሚፈልግ ማንኛው ተጫራች፦

ሀ) - በዘርፉ የፀና የንግድ ፍቃድ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርቲፍኬት እና

የዘመኑን ግብር የከፈለ መሆኑ ከግብር ሰብሳቢ መ/ቤት የተሰጠ

የምስክር ወረቀት ክሊራንስ/ በጨረታ መክፈቻ ቀንና ስዓት ማቅረብ የሚችል፡፡

ለ) የዚህ አንቀፅ ፊደል ተራ (ሀ) ድንጋጌ ቢኖርም ግምታዊ ዋጋው ከብር 500 ሽህ በታች የሆነ ማንኛውም ዕቃ ለመግዛት የሚፈልግ ተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርቲፊኬት ማቅረብ አያስፈልግም፡፡

2 በሃራጅ ጨረታ ላይ ለመሳተፍ የሚፈልግ ተጫራች ዘውትር በስራ ሰዓት ሰኞ ሃምሌ 15 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ እስከ ዓርብ ሃምሌ 19/2016 ዓ/ም ከቀኑ 11፡00 የማይመለስ 100 ብር በመክፈል ከሸራሮ ጉምሩክ መቆጣጠሪያ ዓዲነብሪ ኢድ በመገኘት ወይም በመቐለ ጉምሩክ ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር ይህ ማስታወቅያ አየር ላይ ከዋለበት ለተከታታይ 5 ቀናት ሰነድ መውሰድ ይችላሉ፡፡

3. ተጫራቾች ሰነድ ገዝተው ይህ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በሥራ ቀናት ከጠዋቱ 2፡00 እስከ 11፡00 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ ለሽያጭ የቀረቡ ዕቃዎች ከሸራሮ ጉምሩክ መቆጣጠሪያ ጣቢያ ዓዲ ነብሪ ኢድ ውርስ መጋዘን በመምጣት ሳምፕል ናሙና መመልከት ይችላሉ፣

4. ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ የሚያስይዙት በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ ቅርናጫፍ ጽ/ቤት ስም በማሰራት በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ (CPO) ቅድሚያ ማስያዝ ይኖርባቸዋል' የሚያዘው የሲፒኦ መጠን በተመለከተ ለምግብ ንክ እቃዎች 40,000 (አርባ ሺ ብር) ለቤትና ለቢሮ እቃዎች 10,000 (አስር ሺ ብር) አልባሳት 2,000 ሁለት ሺ ብር) ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡

ማሳሰቢያ፡-ሲፒኦ(CPO) በጥሬ ገንዘብ ለማስያዝ የሚቀርብ ጥያቄ የማንቀበል መሆኑን እንገልፃለን፡፡

5. ተጫራቾች በሚከተለው የጨረታ ቀናት (ስኬጁል) መሠረት መጫረት ይችላሉ፡፡

ጨረታው የሚካሄድበ ት ቦታየንብረቱ ዓይነትጨረታው ዓይነትየንብረት መመልከቻ እና ምዝገባ ቀን የጨረታ ሰነድ ከወሰዱ ቀን ጀምሮየጨረታው መክፈቻ ቀን ና ሰዓት
እስከ
አዲ ነብር ኢድየተለያዩ ዕቃዎችጨረታ ሃራጅ15/11/201619/11/16ከቀኑ 11:00 20/11 /2016 3፡00 ሰዓት ይጀመራል

6. የጨረታ የሚካሄድበት ቦታ በአዲ ነብሪ ኢድ ሲሆን ጨረታው ተጫራቾች ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባለበት ይከፈታል፡፡

7. ለጨረታ አሸናፊ ተጫራቾች ለጨረታው ዋስትና ያስያዙት ሲፒኦ ከሚከፍሉት ዋጋ ጋር የሚታሰብላቸው ሲሆን ለተሸናፊ ተጫራቾች ደግሞ ያስያዙት የጨረታ ዋስትና በ3 ቀናት ወስጥ ተመላሽ ይደረግላችዋል፡፡

8. የጨረታው አሸናፊ ጨረታውን ለማሸነፉ በደብዳቤ ከተገለፀበት ጊዜ ጀምሮ 5(አምስት ቀናት ውስጥ ያሸነፈውን ዕቃ ዋጋ ገቢ በማድረግ ዕቃውን መረከብ አለበት፡፡

9. ከላይ በተ/ቁ 8 በተገለጹት ቀናት ውስጥ ክፍያውን ገቢ ያላደረጉ ከምሽ ተረክበው ያልወሰዱ ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት ዋስትና ለቅ/ጽ/ቤቱ ገቢ ሆኖ ዕቃው በድጋሜ ለሽያጭ ይቀርባል፡፡

10. ቀፅ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገን ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ ሊሰርዝ ይችላል፡፡ 

ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር ኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ መቐለ ቅርንጫፍ ጻ ቤት +251342407107 ወይም +251342408513/ በመደወል ተጨማሪ መረጃ ማግኘት የምትችሉ መሆኑ እንገልፃለን፡፡