ዘ ዳውተርስ ቻሪቲይ

የግልጽ ጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ ማስታወቂያ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏

የፍቅር ልጆች ማህበር /Daughters of Charity / ትግራይ ማስተባበርያ ጽ/ት ቤት የኢትዮጵያ ካቶሊክዊት ቤተክርስትያን - ልማትና ማህበራዊ ኮሚሽን ዓዲግራት ቅርንጫፍ/ Ethiopian Catholic Church Social and Development Commission of Adigrat Branch/ ስር ሆኖ ለሚሰራቸው የተለያዩ የልማት ፣ ማህበራዊና ሌሎች የሰብአዊ አገልግሎቶች እርዳታ እየሰጠ ይገኛል። ከሜርስ ሚልስ ዓለም አቀፍ በጎ አድራጎት ድርጅት/MM/ ጋር በመተባበር በ2 ወረዳዎች ለሚገኙ ትምህርት ቤቶች ያሉ በርካታ ተማሪዎች የሀገር ምርት በሆነ የምግብ ዓይነት በቀን አንድ ግዜ የመመገብ ስራ በመስራት ላይ ይገኛል፡፡ በተመሳሳይ መልኩ ለተለያዩ የቤተሰብ መሪዎች በተመሳሳይ መልኩ ለተለያዩ ቁሳቁሶች ድጋፍ በማድረግ ላይ ይገኛል።

ድርጅታችን ለተማሪዎች የምገባ ፕሮግራምና የምግብ እጥረት ላለባቸው ሴቶችና ህፃናት አገልግሎት የሚውል ፋፋ /famix MS 5%/ በግልፅ ጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ አወዳድረን ለመግዛት ሰለፈለግን ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ፋብሪካዎች እንድትወዳደሩ ጥሪያችንን እናቀርባለን::

  1. ፋፋ/famix ms 5% / ለማምረት የ2016 ዓ.ም የታደሰ ፍቃድ ያላችሁ።
  2. ቫት ተመዝጋቢ የሆነ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያለውና ህጋዊ ተከታታይ ደረሰኝ ማቅረብ የሚችል።
  3. ተጫራቾች ለምርቱ የብቃት ማረጋገጫ ሰርትፍኬትና በቀን ፋፋ የማምረት አቅም ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው።
  4. ተጫራቾች ጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ው ከተከፈተ በኋላ ማስተካከያ ማድረግ ፣ ራስን ከጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ ማግለልም ሆነ መቀየር ኣይቻልም።
  5. ተጫራቾች ውል ከማሰራችን በፊት አጠቃላይ የፋብሪካው ደረጃና የማምረት አቅም ምዘና እንደምናካሂድ ማወቅ ይኖርባቸዋል።
  6. ተጫራቾች ጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ ማስከበርያ በCPO 50,000 ብር በድርጅታችን ስም አሰርተው ከጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ ሰነዱ ጋር ማቅረብ አለባቸው።
  7. ጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ውን ያሸነፈ ዋጋ ፀንቶ የሚቆየው ውል ካሰረበት ቀን ጀምሮ ለስድስት ወር መሆኑ ማወቅ አለባቸው።
  8. ተጫራቾች ውል የሚያስሩት ለአንድ ኩንታል ቢሆንም በሚታዘዘው መጠን /order/ መሰረት የተጠየቀውን ሁሉ በ10 ተከታታይ ቀናት ውስጥ የማቅረብ ግዴታ አለባቸው።
  9. ጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ ያሸነፈው ምርቱ አዲስና ቢያንስ 6 ወር የአገልግሎት ግዜ ያለው በውስጥ ደረጃውን የጠበቀ ፕላስቲክ ከላይ ደረጃውን የጠበቀ በ50 ኪ/ግ ማሸግያ በመጠቀም የድርጅታች 3 ሎጎዎችንና ባች ቁጥር በማተም ማቅረብ የሚችል።
  10. ተጫራቾች የጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ ሰነድ መቀለ ዓዲሓቂ ክፍለ ከተማ የዓይን ህክምና በስተጀርባ የሚገኘው የፍቅር ልጆች ማህበር ትግራይ ክልል ማስተባበርያ ጽ/ት ቤት 5/11/2016ዓም ጀምሮ እስከ 16/11/2016 ዓ.ም ድረስ መውሰድ ይችላሉ :
  11. ጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ው በ16/11/2016 ከቀኑ 8:30 ተዘግቶ በተመሳሳይ ቀን 9:00 ሰዓት‍‍‍‍‌‍‌‍‌‌‌‍‍‍‌‍ ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። ሆኖም ተጫራቾች ባይኖሩም ጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ው ይከፈታል።
  12. የፍቅር ልጆች ማህበር ትግራይ ማስተባበርያ ጽ/ት ቤት ጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።

ማሳሰቢያ- የዋጋ ማቅረቢያ ቅጅ ከጽ/ቤቱ መውሰድ ይቻላል፡፡

የፍቅር ልጆች ማህበር /Daughters of Charity/ ትግራይ ማስተባበርያ ጽ/ት ቤት የኢትዮጵያ

ካቶሊክዊት ቤተክርስትያን-ልማትና ማህበራዊ ኮሚሽን ዓዲግራት ቅርንጫፍ/