ቤት ፅሕፈት ትልምን ፋይናስን ከተማ ዓዲግራት

ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

የዓዲግራት ከተማ ዕቅድና ፋይናንስ ጽሕፈት ቤት ለሴፍትኔት ፕሮግራም የሙያ ግንባታ ሥራ ማስፈፀሚያ ግልጋሎት የሚውል በሎት-1 የተማሪዎች የመማሪያ ክፍል የግንባታ ሥራ በቀበሌ 06፣ በሎት -2 የቴሌ ታወር እና የግሪነሪ አጥር ግንባታ ሥራ በቀበሌ 01፣ በሎት-3 በቪዥን ላይብረሪ የግሪነሪ አጥር ግንባታ ሥራ በቀበሌ 01 በሴፍትኔት ለፕሮጀክት ማስፈፀሚያ ተብሎ ከፀደቀ በጀት በሀገራዊ ግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ግዥ ለመፈፀም ስለሚፈልግ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ለምታሟሉ ባለሙያዎች እንድትወዳደሩ ይጋብዛል።

  • ተጫራቾች የታደሰ ንግድ ፍቃድ ፣ የንግድ ምዝገባ መለያ ቁጥር /Tin No/፣ የዘመኑ የታደሰ የአቅራቢነት ሰርተፊኬት/በኦንላይን በፌዴራል በአቅራቢነት ዝርዝር የተመዘገበበት ማስረጃ/፣ የቫት ምዝገባ ሰርተፊኬት፣ ጊዜው ያላለፈበት የቫት ዲክላሬሽን እና የኮንስትራክሽን የብቃት ማረጋገጫ ቅጂ ከዋናው ዶኩመንት ጋር ማቅረብ የምትችሉ።
  • ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነድ ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ሚያዝያ 6 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ግንቦት 5 ቀን 2018 ዓ.ም 11:30 ሰዓት የማይመለስ በኢትዮጵያ ገንዘብ 500.00/ አምስት መቶ ብር/ እየከፈላችሁ ከዓዲግራት ከተማ ዕቅድና ፋይናንስ ጽሕፈት ቤት በግዥ ቢሮ ቁጥር 7 የጨረታ ሰነድ መውሰድ ትችላላችሁ።
  • ተጫራቾች የጨረታ ሳጥን ከመከፈቱ በፊት በሎት-1 የሙያ የተማሪዎች የመማሪያ ክፍል የግንባታ ሥራ በኢትዮጵያ ገንዘብ 200000.00/ ሁለት መቶ ሺህ ብር/፣ በሎት -2 የቴሌ ታወር እና የግሪነሪ አጥር ግንባታ ሥራ ብር 20000.00 /ሃያ ሺህ ብር/፣ በሎት-3 በቪዥን ላይብረሪ የግሪነሪ አጥር ግንባታ ሥራ ብር 20000.00/ሃያ ሺህ ብር/ በባንክ የተረጋገጠ የባንክ ክሬዲት ሌተር፣ በሲፒኦ ወይም በጥሬ ገንዘብ የጨረታ ማስከበሪያ ማስያዝ አለባችሁ።
  • የጨረታ ሳጥን በከተማ ዓዲግራት ዕቅድና ፋይናንስ የሚገኝ ሲሆን ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተጫራቾች ክፍት ይሆናል።
  • ጨረታው ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ታሽጎ በተመሳሳይ ቀን ከጠዋቱ 4:30 ሰዓት በዓዲግራት ከተማ ዕቅድና ፋይናንስ ጽሕፈት ቤት ተጫራቾች ወይም ወኪላቸው በተገኙበት ይከፈታል።
  • የሚሞላው ዋጋ ስርዝ ድልዝ መኖር የለበትም ስርዝ ድልዝ ካጋጠመ የባለቤቱ ፊርማ መደረግ አለበት
  • የሚሞላው ዋጋ ከነቫቱ መሆኑና አለመሆኑን ሊገለፅ ይገባል፤ ካልተገለፀ ደግሞ የተሞላው ዋጋ ግዥ ፈፃሚ አካል ከነቫቱ መሆኑን ታሳቢ ያደርጋል።
  • በእያንዳንዱ የመጫረቻ ሰነድ ማህተምና ፊርማ የባለቤቱ ተደርጎበት ቴክኒካልና ፋይናንሻሉን ተብሎ ለየብቻው ታሽጎ በሁለት ኮፒ ተደርጎ ማቅረብ አለበት።
  • መሥሪያ ቤታችን ይህ ጨረታ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
  • ለተጨማሪ ማብራሪያ በሥራ ሰዓት በአካል ወደ ቢሯችን በመምጣት ወይም በሞባይል ቁጥር 0914 123 546 ወይ 0941 336 816 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል።

የዓዲግራት ከተማ ዕቅድና ፋይናንስ ጽሕፈት ቤት