ድርጅታችን መከላኪያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ የመቐለ ባለ ሦስት ኮከብ ሆቴል ፕሮጀከት ደረጃውን የጠበቀ ቀይ ኣሸዋ ለመግዛት ስለሚፈልግ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ከቀን 20/02/2011 ዓ/ም ጀምሮ እሰከ 26/02/2011ዓ/ም ከጧቱ 4:00 ድረስ የምትወዳደሩበት ሙሉ ሰነድ በጨረታ ሳጥን በማስገባት እንድትወዳደሩ እየጋበዝን ጨረታውን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በቀን 26/02/2011 ዓ/ም ከጧቱ 4:00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ቀን 4:30 ሰዓት የሚከፈት መሆኑን እየገለፀን ተጫራቸች ማሟላት የሚገባቸውን መመዘኛዎች ከ1-6 ተራ ቁጥር የተገለፁ ነጥቦች ይሆናሉ።
  • Posted Date: ሮብ ጥቅምት 21, 2011 (over 5 years ago)
  • Closing Date: ሰኞ ጥቅምት 26, 2011 04:00 Morning (closed)
  • Bid Bond:5000.00
  • location: መቐለ
  • Bid Document Price:0.00
  • Bid Opening Date: ሰኞ ጥቅምት 26, 2011 04:30 Morning
  • Warehouse and Store/
  • Print
  • Pdf

ተጫራቾች ማሟላት የሚገባቸው ነጥቦች

1 የዘመኑ ግብር የከፈሉ፣ የቫት ተመዝጋቢ የሆኑ፣ እና በዘርፉ ያቅራቢነት ምስክር ወረቀት ማቅረብ የምትችሉ

2  ቲን TIN NO የተመዘገቡበትን ሰርተፊኬት ኮፒ ማቅረብ የምትችሉ

3 የጨረታ ማስከበሪያ ስፒኦ ብር 5000.00 ማስያዝ ይኖርባቸዋል

4 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪላቸው ከሌሉ የሚያስገቡት ዋጋ ዶኩሜንት ኣይከፈትም።ወይም በሌለንበት ይከፈትልን የሚል ፊርማ በማህተም ተደግፎ ሊደርግለት ይገባል።

5 የሚያስገቡት ዋጋ ላይ በሰነዱ ላይ ስርዝ ድልዝ ካለዉ ተወዳዳሪው ከጨረታው ውጭ ይሆናል።

6 የሚያስገቡት ዋጋ ከቫት በፊት ወይም ከቫት በኃላ መሆኑ በግልፅ መቀመጥ ኣለበት። ይህ ካልሆነ ግን ዋጋው ከነቫቱ እንደሆነ ይወሰዳል።

ማሳሰቢያ:-  ፕሮጀክቱ የተሻለ  ኣማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ሆነ በከፊል ጨረታዉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ

 ኣድራሻ ኣክሱም ሆቴል ፊት ለፊት የድሮ ደጀን ሆስፒታል ግቢ ቢሮ ኣሰተዳደር

ስልክ ቁጥር 0344-400242 ወይም 0910-280150

Backs
Tender Category