የኢትዩያ ኦርተዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የልማት ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን የትግራይ ኣህጉር ስብከት ልማት ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት አቡነ መርሃ የገ/ኑ/ማ ፕሮጀክት አገልግሎት እንዲዉሉ የተገዙት ኣምስት ኮምፒተሮች ኣንድ ፕሪንተር ኣንድ ቶፕ በፃሃይ ሃይል በቀን ስምንት ሰኣት ኣገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ ይፈልጋል

በዚህ መሰረት የሶላር መሳሪያዎቹን በማቅረብ እንደርታ ወረዳ መንበረቅዱሳን ቀበሌ ባለዉ የሆሆለ ኣንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በመግጠምና ሞክረዉ ለማስረከብ የሚችሉ

1 አቅራቢነት ህጋዊ ፈቃድ ያላቸዉ::

  2 የ 2009 (2010) ዓ/ም ግብር የከፈሉና የዓመት ፍቃድ ያሳደሱ::

3 ተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይ የሆኑና ያለፈዉ ወር ተእታ የከፈሉበት መረጃ ማቅረብ የሚችሉ::

4 ተጫራቾች ከተራ ቁጥር 1-3 የተጠቀሱት መረጃዎች ኦርጅናልን በመያዝ የጨረታ ሰነድ መግዛት አለባቸዉ

5 ተጫራቾች የጨረታዉን ሰነድ በማይመለስ 20.00 / ሃያ ብር/ በመግዛት ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ 10 / አስር / ቀናት ዉስጥ የጨረታ ሰነድ መግዛት ይችላሉ::

6 የጨረታ ማስከበሪያ ብር 3000 /ሰወስት ሺ ብር / የባንክ ዋስትና ወይም CPO ማቅረብ የሚችሉ::

7 ዕቃዉ ዉል ከተፈፀመ ቀን ጀምሮ በ 15 ተከታታይ ቀናት ዉስጥ ማቅረብ የሚችሉ::

8 ተሞልቶ የሚቀርበዉ ሰነድ ስርዝ ድልዝ የሌለበትና በድርጅታችን በተዘጋጀዉ የጨረታ ሰነድ ብቻ ተሞልቶ መቅረብአለበት

9 የጨረታዉ ሰነድ ዋናዉና ቅጂ ለየብቻዉ በስም በታሸገ ኢንቨሎፕ ለጨረታዉ በተዘጋጀ ሳጥን ማስገባት ያስፈልጋል::

10 የጨረታዉ ሳጥን በ 9/12/2010 ዓ/ም ጥዋት 4:00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ዕለት ከጥዋቱ 4:30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት ወይም መገኘት የማይችሉ ከሆነ ሰነዳቸዉን በማሟለት በፖስታቸዉ ላይ ይከፈትልኝ ብለዉ ከፈረሙና የድርጅቱ ማህተም ካደረጉ በሌሉበት በትግራይ አህጉረ ስብከት ልማት ማስተባበሪያ ፅ /ቤት ይክፈታል::

11 ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታዉን በሙሉ ወይም በክፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ::

አድራሻ 05 ቀበሌ ኮነደሚኒየም አጠገብ የኦርቶዶክስ የህፃናት ማሳደጊያ ድርጅት

Backs
Tender Category