የጨረታ ማስታወቂያ
ጨረታ ቁጥር መቐ/ሪ/ን/ማ/01/2018 ሎት-1
የመቐለ ሪጅን ኤሌክትሪክ አገልግሎት ንብረት የሆኑ እስክራፕ ብረታ ብረቶች ባሉበት ሁኔታ እና ቦታ በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
| ሎት | የዕቃው ዓይነት | የሚገኝበት ቦታ | መለኪያ | ብዛት | የጨረታ ማስከበሪያ (CPO) | የጨረታው መዝጊያ ቀን | የጨረታው መክፈቻ ቀን |
| 1 | የተለያዩ እስክራፕ ብረታ ብረቶች | በመቐለ ከተማ ደንበስኮ ፊት ለፊት የሚገኝ ስቶር ቅጥር ግቢ እና ላጪ ኮንክሪት ማምረቻ ግቢ | በኪ.ግ | 100,000 | 150,000.00 | ሐምሌ 29 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:30 | ሐምሌ 29 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 |
ስለሆነም በጨረታው መካፈል የሚፈልግ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ የሆነ ንግድ ፈቃድ ያለው፣ የትኛውም አካል እና ማንኛውም የንግድ ፈቃድ የሌለው ህጋዊ ግለሰብ ከዚህ በታች የተመለከቱትን ነጥቦች በማሟላት ቀርበው መወዳደር ይችላሉ።
- ተጫራቾች ዝርዘር መግለጫ የያዘውን የጨረታ ሰነድ ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የመቐለ ሪጅን 3ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 302 በመቅረብ የማይመለስ ብር 1000 /አንድ ሺህ/ዘወትር በስራ ሰዓት ከፍለው የሚወዱትን ንብረቶች ዝርዝር መረጃ የያዘ የጨረታ ሰነድ መውሰድ ይችላሉ።
- ተጫራቾች ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የጨረታ ሰነድ ገዝተው ዘወትር በስራ ቀናት ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት እስከ 6፡00 ሰዓት፤ ከሰዓት በኋላ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት እስከ 11፡00 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ ንብረቶቹ በሚገኙበት ቦታ ጨረታ የገዙበትን ደረሰኝ ይዘው በመሄድ መመልከት ይችላሉ።
- ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ የሚያቀርቡት “ለመቐለ ሪጅን ኤሌክትሪክ አገልግሎት” (MEKELLE REGION ELECTRIC UTILITY) ተከፋይ የሆነ በባንክ በተረጋገጠ (CPO) ወይም በቅድመ ሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንከ ዋስትና (Bid Security) ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን እና የጨረታ ማስከበሪያቸውን በታሸገ ኤንቨሎፕ ስማቸውን እና የጨረታ ቁጥሩን በመግለጽ ከላይ በተጠቀሰው ቀንእስከ ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ድረስ ብቻ በተጠቀሰው አድራሻ ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው።
- ጨረታው ከላይ በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት ተዘግቶ በዚያኑ ቀን ከቀኑ 9፡00 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በመቐለ ከተማ ፕላኔት ሆቴል ወረድ ብሎ በሚገኝ ዛምራ ህንፃ ላይ የመቐለ ሪጅን ጽ/ቤት 3ኛ ፎቅ ሰፕላይ ቼይን ንብረትና ጠ/አ ቢሮ ቁጥር 304 ይከፈታል።
- ተጫራቾች የሚያቀርቡት ዋጋ 15% ተጨማሪ እሴት ታክስን ጨምሮ መሆን አለበት።
- ተጨማሪ ማብራሪያ ካስፈለገ በስልክ ቁጥር 00342406712 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።
- ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
መመለስ