የጨረታ ማስታወቂያ
ጨረታ ቁጥር መቐ/ሪ/ን/ማ/02/2018 - ሎት-2
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት መቐለ ሪጅን ንብረት የሆኑት የተለያዩ ቀላልና ከባድ ያገለገሉ 7 ተሽከርካሪዎችን ባሉበት ሁኔታ እና ቦታ በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም በጨረታው መካፈል የሚፈልግ ድርጅት ወይም ግለሰብ ተጫራች ከዚህ በታች የተመለከቱትን ነጥቦች በማሟላት ቀርቦ መወዳደር ይችላል፡፡
- ተጫራቾች ዝርዘር መግለጫ የያዘውን የጨረታ ሰነድ ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ከፕላኔት ሆቴል ወረድ ብሎ የሚገኝ የዛምራ ኮንስትራክሽን ሕንፃ ላይ የመቐለ ሪጅን ጽ/ቤት 3ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 302 ቀርበውየማይመለስ ብር 1,000.00 (አንድ ሺህ ብር) በመክፈል ዝርዝር የተሽከርካሪዎች መረጃ የያዘ የጨረታ ሰነድ መውሰድ ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ ገዝተው ዘወትር በስራ ቀናት ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት እስከ 6፡00 ሰዓት ከሰዓት በኋላ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት እስከ 11፡00 ሰዓት ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ ተሽከርካሪዎችን በመቐለ ከተማ 05 ቀበሌ ደንበስኮ ፊት ለፊት የሚገኝ የመቐለ ሪጅን ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዕቃ ግምጃ ቤት ቅጥር ግቢ በመሄድ መመልከት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች ለሚጫረቱበት ተሽከርካሪ ለእያንዳንዱ የጨረታ መነሻ ዋጋ 20 በመቶ (20%) የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ (CPO) ወይም በቅድመ ሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና (Bid Bond) በመቐለ ሪጅን ኤሌክትሪክ አገልግሎት (MEKELLE REGION ELECTRIC UTILITY) ስም ከመወዳደሪያ ሰነዳቸው ጋር በታሸገ ኤንቨሎፕ በማሸግ የጨረታ ቁጥሩን በመግለፅሓምሌ 28 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ድረስ ብቻ በመቐለ ከተማ ከፕላኔት ሆቴል ወረድ ብሎ የሚገኝ ዛምራ ኮንስትራክሽን ህንፃ 3ኛ ፎቅ የመቐለ ሪጅን ሳፕላይ ቼይን ንብረት እና ጠቅላላ አገልግሎት ቢሮ ቁጥር 304 በመምጣት ለጨረታው በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ጨረታውሐምሌ 28 ቀን 2017ዓ.ም ከቀኑ በ8፡30 ሰዓት ተዘግቶ በዚያው ቀን ከቀኑ በ9፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻው በተገኙበት ከላይ በተገለፀው አድራሻ ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች የሚያቀርቡት ዋጋ 15% ተጨማሪ እሴት ታክስን ጨምሮ መሆን አለበት፡፡
- ተጨማሪ ማብራሪያ ካስፈለገ በስልክ ቁጥር 034 240 6712 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።
- ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
መመለስ