የፍቅር ልጆች ማህበር ለተማሪዎች የምገባ ፕሮግራምና የምግብ እጥረት ላለባቸው ሴቶችና ህፃናት አገልግሎት የሚውል ፋፋ /famix MS 5%/ በግልጽ ጨረታ አወዳድረን ለመግዛት ይፈልጋል
  • Posted Date: ሮብ ሐምሌ 24, 2016 (about 1 month ago)
  • Closing Date: ሰኞ ሐምሌ 29, 2016 08:30 Afternoon (closed)
  • Bid Bond:50,000
  • location: መቐለ
  • Bid Document Price:
  • Bid Opening Date: ሰኞ ሐምሌ 29, 2016 09:00 Afternoon
  • Food Items Supply/
  • Print
  • Pdf

ለ2ኛ ጊዜ የወጣ የግልጽ ጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ ማስታወቂያ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏

የፍቅር ልጆች ማህበር (Daughters of Charity/ ትግራይ ማስተባበሪያ ጽ/ት ቤት የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስትያን - ልማትና ማህበራዊ ኮሚሽን ዓዲግራት ቅርንጫፍ /Ethiopian Catholic Church Social and Development Commission of Adigrat Branch/ ስር ሆኖ ለሚሰራቸው የተለያዩ የልማት ፣ ማህበራዊና ሌሎች የሰብኣዊ አገልግሎቶች እርዳታ እየሰጠ ይገኛል። ከሜርስ ሚልስ ዓለም አቀፍ በጎ አድራጎት ድርጅት /MM1/ ጋር በመተባበር በ12 ወረዳዎች ለሚገኙ ትምህርት ቤቶች ያሉ በርካታ ተማሪዎች የሀገር ምርት በሆነ የምግብ ዓይነት በቀን አንድ ግዜ የመመገብ ስራ በመስራት ላይ ይገኛል። በተመሳሳይ መልኩ ለተለያዩ የቤተሰብ መሪዎች የምግብና የተለያዩ ቁሳቀቁሶች ድጋፍ በማድረግ ላይ ይገኛል።

ድርጅታችን ለተማሪዎች የምገባ ፕሮግራምና የምግብ እጥረት ላለባቸው ሴቶችና ህፃናት አገልግሎት የሚውል ፋፋ /famix MS 5%/ በግልጽ ጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ አወዳድረን ለመግዛት ስለፈለግን ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ፋብሪካዎች እንድትወዳደሩ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

  1. ፋፋ/famix ms 5%/ ለማምረት የ2016 ዓ.ም የታደሰ ፈቃድ ያላችሁ፡፡
  2. ቫት ተመዝጋቢ የሆነ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያለውና ህጋዊ ተከታታይ ደረሰኝ ማቅረብ የሚችል።
  3. ተጫራቾች ለምርቱ የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬትና በቀን ፋፋ የማምረት አቅም ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው።
  4. ተጫራቾች ጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ው ከተከፈተ በኋላ ማስተካከያ ማድረግ ፣ ራስን ከጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ ማግለልም ሆነ መቀየር አይቻልም፡፡
  5. ተጫራቾች ውል ከማሰራችን በፊት አጠቃላይ የፋብሪካውን ደረጃና የማምረት አቅም ምዘና እንደምናካሂድ ማወቅ ይኖርባቸዋል።
  6. ተጫራቾች የጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ ማስከበሪያ በCPO 50,000 ብር በድርጅታችን ስም አሰርተው ከጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ ሰነዱ ጋር ማቅረብ አለባቸው።
  7. ጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ውን ያሸነፈ ዋጋ ፀንቶ የሚቆየው ውል ከታሰረበት ቀን ጀምሮ ለስድስት ወር መሆኑን ማወቅ አለባቸው።
  8. ተጫራቾች ውል የሚያስሩት ለአንድ ኩንታል ቢሆንም በሚታዘዘው መጠን /order/ መሰረት የተጠየቀውን ሁሉ በ ተከታታይ ቀናት ውስጥ የማቅረብ ግዴታ አለባቸው።
  9. ጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ ያሸነፈው ምርቱ አዲስና ቢያንስ 6 ወር የአገልግሎት ግዜ ያለው በውስጥ ደረጃውን የጠበቀ ፕላስቲክ ከላይ ደረጃውን የጠበቀ በ50 ኪ/ግ ማሸጊያ በመጠቀም የድርጅታች 3 ሎጎዎችንና ባች ቁጥር በማተም ማቅረብ የሚችል።
  10. ተጫራቾች የጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ ሰነድ መቐለ ዓዲሓቂ ክፍለ ከተማ የዓይን ህክምና በስተጀርባ የሚገኘው የፍቅር ልጆች ማህበር ትግራይ ክልል ማስተባበሪያ ጽ/ት/ቤት ወይም አዲስ አበባ አራዳ ክ/ከተማ ወረዳ 1 የቤት ቁጥር 374 ካቴድራል ት/ት ቤት ጎን 19/11/2016 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 30/11/2016 ዓ.ም ድረስ በመውሰድ መቐለ ማስተባበሪያ ፅ/ቤት ለዚሁ በተዘጋጀ የጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል።
  11. ጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ው በመቐለ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት በ30/11/2016 ከቀኑ 8:30 ተዘግቶ በተመሳሳይ ቀን 9፡00 ሰዓት‍‍‍‍‌‍‌‍‌‌‌‍‍‍‌‍ ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። ሆኖም ተጫራቾች ባይኖሩም ጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ው ይከፈታል።
  12. የፍቅር ልጆች ማህበር ትግራይ ማስተባበሪያ ጽ/ት/ቤት ጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።

የፍቅር ልጆች ማህበር ትግራይ ማስተባበሪያ ጽ/ት ቤት

Backs
Tender Category