በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን በመቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የሚገኙ የተወረሱ እቃዎች ማለትም አልባሳት፤ ሸቀጣሸቀጦችና የቤት እቃዎች ባሉበት ቦታና ሁኔታ ብሓራጅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሽጥ ይፈልጋል፡፡
  • Posted Date: ኣርብ ሐምሌ 12, 2016 (2 months ago)
  • Closing Date: ሓሙስ ሐምሌ 18, 2016 06:00 Morning (closed)
  • Bid Bond:የጨረታ ማስከበሪያ በሎት/ምድብ/ ይለያያል
  • location: መቐለ
  • Bid Document Price:100.00
  • Bid Opening Date: ሓሙስ ሐምሌ 18, 2016 07:15 Afternoon
  • Other Sale/ Used Items Sale/
  • Print
  • Pdf

ቁጥር 14/2016

የሃራጅ ጨረታ ማስታወቅያ

በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን በመቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የሚገኙ የተወረሱ እቃዎች ማለትም አልባሳት፤ ሸቀጣሸቀጦችና የቤት እቃዎች ባሉበት ቦታና ሁኔታ ብሓራጅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሽጥ ይፈልጋል፡፡

1. በመሆኑ ቅ/ፅ/ቤቱ ባወጣው የዕቃ ሽያጭ ጨረታ መወዳደር የሚፈልግ ማንኛው ተጫራች፦

ሀ) በዘርፉ የፀና የንግድ ቁጥር የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርቲፍኬት እና የዘመኑን ግብር የከፈለ መሆኑ ከግብር ሰብሳቢ መ/ቤት የተሰጠ ማስረጃ ኮፒ ማቅረብ የሚችል፡፡

ለ) የዚህ አንቀፅ ፊደል ተራ (ሀ) ድንጋጌ ቢኖርም ግምታዊ ዋጋው ከብር 500 ሽህ በታች የሆነ ማንኛውም ዕቃ ለመግዛት የሚፈልግ ተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርቲፊኬት ማቅረብ አያስፈልግም::

2. በሃራጅ ጨረታ ለመሳተፍ የሚፈልግ ተጫራች ዘውትር በስራ ሰዓት ከሮብ ሃምሌ

10 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ እስከ ሃምሌ ሓሙስ 18 ቀን 2016 ዓ/ም ከቀኑ 6፡00 ሰዓት በቅ/ጽ/ቤቱ ገቢ ሰብሳቢ እና ዋስትና አያያዝ ቡድን ገንዘብ ያዥ ቢሮ 104 በመቅረብ የማይመለስ ብር 100(አንድ መቶ ብር) በመክፈል የጨረታ ሰነድ ከዕቃ አወጋገድ ቡድን ከኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 406 መውስድ ይችላሉ፡፡

3. ተጫራቾች ሰነድ ገዝተው ይህ ማስታወቂያው ከጠዋቱ 2፡00 እስከ 11፡00 ሰዓት ባለው ጊዜ የውርስ መጋዘን በመምጣት መመልከት ይችላሉ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በሥራ ቀናት ውስጥ ለሽያጭ የቀረቡ ዕቃዎች በመቐለ ቅ/ፅ/ቤት

4. ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ የሚያስይዙት ሲፒኦ (CPO) በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ ቅርናጫፍ ጽ/ቤት ስም በማሰራት ቅድሚያ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡ የሚያዘው የሲፒኦ መጠን በተመለከተ ለምድብ 01 አልባሳት 3000 ብር ፤ ለምድብ 02 በትንሽ ሱቅ የሚሸጡ እቃዎች ብር 5000 ለምድብ 03 የቤት እቃዎች ብር 3000 ማስያዝ ይኖርባቸዋል''

5. ተጫራቾች በሚከተለው የጨረታ ቀናት (ስኬጁል) መሠረት መጫረት ይችላለ፡

ጨረታው የሚካሄድበት ቦታየንብረቱ ዓይነትጨረታ ዓይነትየንብረት መመልከቻ እና ጨረታው ምዝገባ ቀን የጨረታ ሰነድ ከወሰዱ ቀን ጀምሮየጨረታው መክፈቻ ቀን ና ሰዓት
እስከ
መቐለ ጉ/ቅ/ጽ/ቤየተለያዩ ዕቃዎችሃራጅ ጨረታ10/11/201618/11/16 ከቀኑ 6፡00 ሰዓት18/11 /2016 7:15 ሰዓት ይከፈታል፡፡

6. የጨረታ መክፈቻ ቦታ መቐለ ጉ/ቅ/ጽ/ቤት የሚካሄድ ሲሆን ጨረታው ተጫራቾች/ህጋዊወኪሎቻቸው ባሉበት ይከፈታል::

7. ለጨረታ አሸናፊዎች ተጫራቾች ለጨረታው ዋስትና ያስያዙት ሲፒኦ ከሚከፍሉት ዋጋ ጋር የሚታሰብላቸው ሲሆን ለተሸናፊ ተጫራቾች ያስያዙት የጨረታ ዋስትና በ3 ቀናት ወስጥ ተመላሽ ይደረግላችዋል::

8. የጨረታው አሸናፊ ጨሪታውን ለማሸነፉ ከተገለጸለት ጊዜ ጀምሮ 5(አምስት) ቀናት ውስጥ ያሸነፈበት ዕቃ ዋጋ ገቢ በማድረግ ዕቃውን መረከብ አለበት፡፡

9. ከላይ በተ/ቁ 7 በተገለጹት ቀናት ውስጥ ክፍያውን ገቢ ያላደረጉ እና ንብረቱን ተረክበው ያልወሰዱ ተጫራቶች ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት ዋስትና ለቅ/ጽ/ቤቱ ገቢ ሆኖ ዕቃው በደጋሜ ለሽያጭ ይቀርባል፡፡

10. ቅ/ፅ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ ሊሰርዝ ይችላል፡፡ ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር ኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ መቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት +251342407107 ወይም +251342408513/ በመደወል ተጨማሪ መረጃ ማግኘት የምትችሉ መሆኑ እንገልፃለን፡፡

Backs
Tender Category