በኢትዮጵያ ምርጥ ዘር አቅርቦት መቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የተለያዩ እህልና ብጣሪ በጨረታ መሸጥ ይፈልጋል።
  • Posted Date: ሮብ ጥቅምት 14, 2016 (11 months ago)
  • Closing Date: ማክሰኞ ጥቅምት 20, 2016 03:30 Morning (closed)
  • Bid Bond:5%
  • location: መቐለ
  • Bid Document Price:50.00
  • Bid Opening Date: ማክሰኞ ጥቅምት 20, 2016 04:00 Morning
  • Food Items Supply/
  • Print
  • Pdf

ለ2ኛ ጊዜ የወጣ ጨረታ ማስታወቂያ

በኢትዮጵያ ምርጥ ዘር አቅርቦት መቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የተለያዩ እህልና ብጣሪ በጨረታ መሸጥ ይፈልጋል። በመሆኑም በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ በዘርፉ የንግድ ፍቃድ ያላቸው እና የዘመኑን ግብር ለመክፈላቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ ተጫራቾች ዘወትር በሥራ ሰዓት በቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ የማይመለስ ብር 50.00 በመክፈል የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡

ጨረታው ጥቅምት 20ቀን 2016 ዓ.ም ከጧቱ 3፡30 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ቀን 4፡00 ሰዓት በቅርንጫፍ ጽ/ቤት ይከፈታል። ስለዚህ ሽያጭ አፈጻጸሙ በጨረታ ሠነዱ በተገለፀው መሠረት የሚፈጸም መሆኑን እየገለጽን፣ ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና/ቢድ ቦንድ/ የጠቅላላ የጨረታ ዋጋውን 5% በሲፒኦ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡

ተጫራቾች ከላይ የተገለፀውን መጠን በሙሉ ወይም በከፊል መጫረት ይችላሉ፡፡ ድርጅቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። ለተጨማሪ ማብራሪያ በሚቀጥለው አድራሻ መጠቀም ይቻላል፡፡

በኢትዮጵያ የግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን መቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት

Backs
Tender Category