https://tenders.milkta.com/am/tenders/display/8962
የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ ከዚህ በታች የተጠቀሱትን የተለያዩ ዕቃዎችና አገልግሎቶች ማለትም፡- የመኪና መለዋወጫ እቃዎች፣ የጽሕፈት መሣሪያዎች፣ የፅዳት እቃዎች፣የቢሮ እቃዎች /ፈርኒቸር/፣ የአይቲ ኤሌከትሮኒክስ እቃዎች፣ ሕትመት በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል
  • የተለቀቀበት ቀን: ቀዳም ጥቅምቲ 8, 2012 (ከ 6 ዓመታት)
  • መዝግያ ቀን: ረቡዕ ጥቅምቲ 26, 2012 03:29 ጥዋት (ተዘጋ)
  • የጨረታ ማስከበርያ ዋጋ:00
  • ቦታ:መቐለ
  • የጨረታ ደኩመንት ዋጋ:100
  • ጨረታ ሚከፈትበት ቀንና ሰዓት: ረቡዕ ጥቅምቲ 26, 2012 03:30 ጥዋት
  • ምድብ: መለዋወጢ ኣቁሑት ተሸከርከርቲ/ ናይ ንፅህናን ፅሬት ኣቁሑት/ ናይ ኮምፒተር ተዛመድቲ አቁሑትን/ ኤሌክትሮኒክስ መሳርሕታትን መለዋወጢን/ ናይ ቢሮ ፈርኒቸር/ ናይ ፅሕፈት መሳሪሕታተት/ ናይ ሕትመት ስራሕቲ/
  • ሎት 1. የመኪና መለዋወጫ እቃዎች፣ 
  • ሎት 2. የጽሕፈት መሣሪያዎች፣ 
  • ሎት 3 የፅዳት እቃዎች፣ 
  • ሎት 4 የቢሮ እቃዎች /ፈርኒቸር/፣ 
  • ሎት 5. የአይቲ ኤሌከትሮኒክስ እቃዎች፣ 
  • ሎት 6. ሕትመት በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል:: 

በመሆኑም በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ በዘርፉ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላችሁ አቅራቢ ድርጅቶች በጨረታው እንድትሳተፉ እየጋበዝን፤ የተዘጋጀው የጨረታ ዶኩሜንት ለእያንዳንዱ የማይመለስ ብር 100.00 በመክፈል ጀምሮ ሕጋዊ የንግድ ፈቃዳችሁን በመያዝ ከቢሮኣችን የዕቃ ግዥ ክፍል ቢሮቁጥር 2 በሥራ ሰዓት እየመጣችሁ መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን፤ በጨረታው ለመሳተፍ ቀጥለው የተዘረዘሩትን ማሟላት ያስፈልጋል::  

  • የዘመኑ የታደሰ ንግድፈቃድ፣ የአቅራቢዎች ምዝገባ ሰርተፊኬት፣ የVAT ሠርቲፊኬት፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር (TIN) እና ያለፈው ወር ቫት (VAT) ዲክለር የተደረገበት ማስረጃ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አብሮ መቅረብ አለበት:: 
  • ተጫራቾች የጨረታ መመሪያውን በጥንቃቄ አይተው መወዳደር አለባቸው። 
  • የጨረታ ማስከበሪያ ቢድ ቦንድ በጨረታ ዶክመንቱ ላይ የተጠቀሰውን መጠን ገንዘብ በ(CPO) አሠርተው ጨረታው ከመከፈቱ በፊት አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል:: ቢሮአችን በጨረታ ከቀረበው የዕቃዎች ብዛት እስከ 20% የመጨመር ወይም የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው። 
  • ጨረታው ጥቅምት 26/2012 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡30 ሰዓት ተዘግቶ ወዲያውኑ መገኘት የሚፈልጉ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በቢሮአችን የዕቃ ግዥ ክፍል ይከፈታል። 
  • *ቢሮአችን የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታው ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። 

ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥሮች 034 44036 63/ 034 440 43 46 ወይም በፋክስ ቁጥር 034 440 99 71/034 440 36 63 መጠየቅ ይቻላል። 

የትግራይ ክልል ግብርናና 

ገጠር ልማት ቢሮ