https://tenders.milkta.com/am/tenders/display/5040
የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ የፀረ ተባይ ኬሚካል፣የጓሮ አትክልት ዘር፣የማር ሰም ፣ሞተር ሳይክል፣የእንስሳት መድሃኒትና መገልገያ መሳሪያዎች፣የንብ መገልገያ መሳሪያዎች፣የቢሮ እቃዎች /ፈርኒቸር/ በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል
  • የተለቀቀበት ቀን: ሓሙስ ጥቅምቲ 1, 2011 (ከ 7 ዓመታት)
  • መዝግያ ቀን: ሶኒ ጥቅምቲ 12, 2011 09:30 ከሰአት (ተዘጋ)
  • የጨረታ ማስከበርያ ዋጋ:00
  • ቦታ:መቐለ
  • የጨረታ ደኩመንት ዋጋ:100
  • ጨረታ ሚከፈትበት ቀንና ሰዓት: ሶኒ ጥቅምቲ 12, 2011 09:31 ከሰአት
  • ምድብ: ስራሕቲን ውፅኢት ሕርሻ/ ሕርሻ መሺነሪ/ ፍዮሪን ሆልቲካልቸር/ ናይ ቢሮ ፈርኒቸር/ ኬሚካልን ሪኤጀንት/ ናይ እንስሳት ምድሃኒታትን መሳሪሕታትን/ ዕድጊት ሞተርሳይክል/

ሎት 1. የፀረ ተባይ ኬሚካል

ሎት 2. የጓሮ አትክልት ዘር

ሎት 3. የማር ሰም

ሎት 4. ሞተር ሳይክል

ሎት 5. የእንስሳት መድሃኒትና መገልገያ መሳሪያዎች

ሎት 6. የንብ መገልገያ መሳሪያዎች

ሎት 7. የቢሮ እቃዎች /ፈርኒቸር/

1 በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል። በመሆኑም በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ በዘርፉ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላችሁ አቅራቢ ድርጅቶች በጨረታው እንድትሳተፉ እየጋበዝን፣ የተዘጋጀውን የጨረታ ዶኩሜንት ለያንዳንዱየማይመለስ ብር 100.00 በመክፈልጀምሮ ሕጋዊ የንግድ ፈቃዳችሁን በመያዝ ከቢሮአችን የዕቃ ግዥ ክፍል ቢሮ ቁጥር 12 በሥራ ሰዓት እየመጣችሁ መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን፣ በጨረታው ለመሳተፍ ቀጥለው የተዘረዘሩትን ማሟላት ያስፈልጋል።

2 የዘመኑን የታደሰ ንግድ ፈቃድ፣ የአቅራቢዎች ምዝገባ ሰርተፊኬት፣ የVAT ሰርተፊኬት፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር (Tin) እና ያለፈው ወር ቫት (VAT) ዲክለር የተደረገበት ማስረጃ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አብሮ መቅረብ አለበት። ተጫራቾች የጨረታ መመሪያውን በጥንቃቄ አይተው መወዳደር አለባቸው።

3 የጨረታ ማስከበሪያ ቢድ ቦንድ በጨረታ ዶኩመንቱ ላይ የተጠቀሰው መጠን ገንዘብ በCPO አሰርተው ጨረታው ከመከፈቱ በፊት አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል።

4 ቢሮአችን በጨረታ ከቀረበው የዕቃዎች ብዛት እስከ 20% የመጨመር ወይም የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው።

5 ጨረታውበ 12/2/2011 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡30 ሰዓት ተዘግቶ ወዲያውኑ መገኘት የሚፈልጉ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በቢሮአችን የዕቃ ግዥ ክፍል ይከፈታል።

6 ቢሮአችን የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

7 ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥሮች 03 44 40 36 63/03 44 40 43 46 ወይም በፋክስ ቁጥር 03 44 40 99 71/ 03 44 40 36 63 መጠየቅ ይቻላል