ደደቢት ብድርና ቁጠባ ተቋም ዓ/ማ 2010 ዓ/ም የደርጅቱን ሒሳብ በጨረታ አወዳድሮ ኦዲት ለማስደረግ ይፈልጋል
  • የተለቀቀበት ቀን: ሓሙስ መስከረም 10, 2011 (ከ 5 ዓመታት)
  • መዝግያ ቀን: ሰኞ መስከረም 14, 2011 03:00 ጥዋት (ተዘጋ)
  • የጨረታ ማስከበርያ ዋጋ:2%
  • ቦታ: መቐለ
  • የጨረታ ደኩመንት ዋጋ:100.00
  • ጨረታ ሚከፈትበት ቀንና ሰዓት: ሰኞ መስከረም 14, 2011 03:30 ጥዋት
  • ኦዲት ተዛማድኡን/ ፋይናንሻል ኮንሳልታንሲይ/
  • Print
  • Pdf

ለሁለተኛ ጊዜ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ

ደደቢት ብድርና ቁጠባ ተቋም ዓ/ማ 2010 ዓ/ም የደርጅቱን ሒሳብ በጨረታ አወዳድሮ ኦዲት ለማስደረግ ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ ለመጫረት የምትፈልጉ የኦዲት ድርጅቶች (Audit Firms) ከዚህ በታች የተጠቀሱትን የምታሟሉ እንድትወዳደሩ እንጋብዛለን፡፡

1. የተጫራቾች የጨረታው ፍቃድና የ2010 ዓ/ም የመንግስት ግብር የከፈሉበትን ማስረጃና ቫት ተመዝጋቢ መሆናቸውን ማቅረብ የሚችሉ፡፡ 

2. ለመጫረት የምትፈልጉ ተወዳዳሪዎች የምትሰሩበትን ዋጋ በስም በታሸገ ኢንቨሎፕ መቐለ ዋና መ/ቤት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን እስከ መስከረም 14/2011 ዓ.ም ከቀኑ 3፡00 ሰዓት ድረስ ማስገባት ትችላላቹህ፡፡ 

3. ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበርያ የሚሆን ከጠቅላላ ዋጋ 2% ለድርጅቱ በባንክ የተረጋገጠ ቼክ (CPO) እስከ መስከረም 14/2011 ዓ.ም ከጥዋቱ 3፡00 ድረስ ገቢ ማድረግ ይኖርባችዋል፡፡ ከ2% በታች ያስያዘ ከጨረታ ዉጭ የሚደረግ ይሆናል፡፡ 

4. ተጫራቾች የጨረታዉ ዶኩሜንትር መቐለ በሚገኘዉ የድርጅቱ ዋና መ/ቤት 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 409 ወይም አዲስ አበባ በሚገኘዉ ተክለሃይማኖት ቅርንጫፋችን ብር 100 በመክፈል ከ04/01/2011 ዓ.ም ጀምሮ በስራ ሰዓት መውሰድ እንደምትችሉ እንገልፃለን፡፡ 

5. በድርጅቱ የቀረበውን ሰነድ ተጫራቶች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበትመስከረም 14/01/2011 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡30 ሰዓት መቐለ በሚገኘዉ ዋና ቢሮ ይከፈታል፡፤   

6. ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ ባይገኙም ጨረታዉ የሚከፈት ይሆናሉ፡፡

7. የጨረታው አሸናፊ የጨረታው ውጤት እንደተገለፀ ከጠቅላላ ዋጋ 10% performance bond ማስያዝ ይኖርበታል፡፡ 

8. የጨረታው ኣሸናፊ የጨረታው ውጤት እንደተገለፀ በ5 ቀን ውስጥ ውል ማሰር ይኖርበታል፡፡ 

9. የድርጅቱ ሒሳብ ስራ በትግርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ ስለሆነ ይህንን ግምት ውስጥ በማስገባት ሊሰሩ የሚችሉ መሆን ይኖርበታል፡፡ 

10. የድርጅቱ ጨረታ በሙሉ ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ 

11. ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁ. 03-44-41-03-96 ደውለው ማረጋገጥ የምትችሉ መሆናችሁን እናሳስባለን፡፡ 

መመለስ
የጨረታ ምድብ