ለበርሃሌ ስደተኞች መጠሊያ ጣቢያ ፅቤት ለሚያስገነባዉ ግንባታ የሚዉል የግንብ ድንጋይ : የኩረት ድንጋይ : ባለ 02 ጠጠር: አሸዋ በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል
  • የተለቀቀበት ቀን: ሓሙስ ሐምሌ 26, 2010 (ከ 6 ዓመታት)
  • መዝግያ ቀን: ማክሰኞ ነሐሴ 1, 2010 04:00 ጥዋት (ተዘጋ)
  • የጨረታ ማስከበርያ ዋጋ:2%
  • ቦታ: መቐለ
  • የጨረታ ደኩመንት ዋጋ:0.00
  • ጨረታ ሚከፈትበት ቀንና ሰዓት: ማክሰኞ ነሐሴ 1, 2010 04:30 ጥዋት
  • መኽዝን/
  • Print
  • Pdf

1 ህጋዊ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸዉ

2 ግብር በወቅቱ ያሳወቁ

3 የጨረታ ማስከበሪያ 2% በ CPO ማስያዝ የሚችሉ

4 ጨረታዉን ማሸነፋ እንደተገለፀለት ወዲያዉኑ ያሸነፈበትን ጠቅላላ ዋጋ 5% ለመልካም አፈፃፀም ዋስተና ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችሉ ተወዳዳሪዎች በሙሉ

5 ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 07 ቀናት እስከ 1/12/2010 ዓ/ም ጠዋት 4:00 ሰዓት ድረስ ዋጋ ማቅረቢያ በመሙላት በታሸገ ኢንቨሎፕ ሙሉ ስምና አድራሻ በመፃፍ በራህሌ በሚገኘዉ የመሰብሰቢያ አደራሽ በተዘጋጀዉ ሳጥን ዉስጥ ማስገባት የሚችሉ መሆኑ እንገልፃለን

6 ጨረታዉ የሚከፈተብት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት መስከረም 1/12/2010 ዓ/ም ከቀኑ 4:00 ታሽጎ በእለቱ 4:30 በበርሃሌ ስደተኛ መጠሊያ ጣቢያ ፅ/ቤት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት በግልፅ ይከፈታል በመሆኑም ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ ካልተገኙ መቤቱ በሌሉበት ጨረታዉን የሚከፈት መሆኑን እንገልፃለን

7 ተጫራቾች ለተጠየቁት ኣቅርቦት በመስሪያ ቤቱ በመጠየቂያ ቅፅ በተጠየቀዉ መሰረት በመጥቀስ PR-No ባለዉ ሰንጠረዥ መሰረት ከተቁ 1 እስከ 4 የተጠየቁትን ኣቅርበቶች ለያይተዉ መሙላት ይኖርባቸዋል

8 ኣሸናፊ ድርጅት ለሚያቀርበዉ ኣቅርቦት የትራንስፕርት አሸዋና ድንጋይ የኣካባቢዉ የማዕድን ክፍያ በራሱ በመክፈል የጉልበት ሰራተኞች በራሱ አቅርቦ በማስጫን ያቀርባል

9 ተጫራቾች ለሚያቀርቡት ስፒኦ ARRA /Berhale Refugee Camp ብለዉ መፃፍ አለባቸዉ

10 መ/ቤቱ የተሻለ ነገር ካገኘ ጨረታዉን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ

በስልክ ቁጥር 0914709899 0936690401ደዉሉዉ መጠየቅ ይችላሉ 

መመለስ
የጨረታ ምድብ