የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር ቲ-07/2017
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዓዲ-ግራት መንገድ ጥገና ዲስትሪክት ለሚያከናውናቸው የተለየዩ የመንገድ ሥራዎች አገልግሎት የሚውሉ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የኮንስትራክሽን መሳሪያዎች በተቀመጠላቸው ቁርጥ ዋጋ መከራየት ስለሚፈልግ ከታች የተዘረዘሩት መስፈርቶችን የሚያሟሉ ብቁ ተጫራቾችን በግልፅ ጨረታ እንዲሳተፉ ይጋብዛል።
1. በጨረታ ለመካፈል የሚፈልጉ ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ የሚያስችል የ2017 ዓ.ም ግብር የከፈለበት ከሚፈልገው ግዥ የተዛመደ የታደሰ ንግድ ሥራ ፈቃድ ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይ መሆናቸውን ማረጋገጫ ሰርተፊኬት እና በጨረታው ለመሳተፍ ከሀገር ውስጥ ገቢዎች ቢሮ ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ በማቅረብ የጨረታ ሰነዱን ዘወትር በስራ ሰዓት ዓዲ-ግራት ከተማ ከሚገኘው ዓዲግራት መንገድ ጥገና ዲስትሪከት በመቅረብ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ማግኘት ይችላሉ።
2. ጨረታው ዜግነትን ሳይመለከት ለማንኛውን ህጋዊ ተጫራች ክፍት ነው፡፡ የጨረታ ሰነድ የተዘጋጀው በአማርኛ ቋንቋ ነው።
3. ተጫራቾች የሚወዳደሩት የጨረታ ዓይነት በቁርጥ ዋጋ ነው።
4. የጨረታው አሸናፊ ቀድሞ የመጣ ቅድሚያ የሚሰጠው ቢሆንም ሁለት(2) እና ከዛ በላይ ተጫራቾች በተመሳሳይ ጊዜ ተመዝግቦ ከተገኙ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት መስከረም 2 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4:30 ሰዓትአዲግራት በሚገኘው የቅርንጫፍ ዋና ቢሮ በመሰብሰቢያ አዳራሽ በዕጣ አሸናፊ ይለያል።
5. የመሳሪያ አከራይ ድርጅቶች ግለሰቦች ህጋዊ ተወካዮች መሣሪያዎችን ለማከራየት በሚመጡበት ወቅት የመሣሪያው ባለቤትነት ደብተር/ሊብሬ ይዘው መምጣት የሚኖሩባቸው ሲሆን መሣሪያው የራሱ ያልሆነ ድርጅቶች ግለሰብ ህጋዊ ተወካይ በጨረታው ላይ መሳተፍ አይቻልም።
6. ለውሃ ቦቴ አከራይ ተጫራቾች ለማከራየት የሚያቀርቡትን የውሃ ቦቴ የስሪት ዘመኑ እ.ኤ.አ ከ2000 ጀምሮ ማቅረብ ይችላሉ፡፡ ነገር ግን ከውሃ ቦቴ ውጭ ያሉ የኪራይ መሣሪያዎች የስሪት ዘመናቸው እ.ኤ.አ ከ2007 ጀምሮ መሆን አለበት።
7. ተጫራቾች በኪራይ የሚያቀርቡት መሣሪያ በዲስትሪክቱ ሥራ ቦታ ላይ መሣሪያውን አጓጉዘው ማቅረብ እንደሚጠበቅባቸውና በሳይት ላይ አግባብነት ባላቸው ባለሙያዎች አማካኝነት ሙሉ የቴክኒክ ብቃት ፍተሻ እንዲያከናውኑ ፍቃደኛ መሆን አለባቸው።
የመሣሪያዎች ዝርዝር
ተ.ቁ | የመሣሪያው ዓይነት | የመሳሪያው አቅም | የኪራይ ዋጋ ተ.እ.ታክስ እና ነዳጅ ጨምሮ | የመሳሪያ ብዛት |
1 | ገልባጭ | >16 m3 | ከ0-5ኪ.ሜ=35.66 ብር ከ5-10ኪ.ሜ=34.19 ብር ከ10-50ኪ.ሜ=32.60 ብር ከ50-100ኪ.ሜ=29.27 ብር ከ100ኪ.ሜ በላይ ከሆነ=26.43 ብር | 9 |
2 | ሎደር | Hp>2.75 m3 | 3,402.01 ብር/ሰዓት | 2 |
3 | ግሬደር | Hp>165 | 4,501.99 ብር/ሰዓት | 3 |
4 | ዶዘር | Hp>285 | 8,527.14 ብር/ሰዓት | 3 |
5 | ውሃቦቲ | >13000 ሊትር | 2,516.67 ብር/ሰዓት | 2 |
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዓዲ-ግራት መንገድ ጥገና ዲስትሪክት
መመለስ