የእንዳሞኾኒ ወረዳ እቅድና ፋናንስ በሴፍትኔት በጀት አሸዋ ጠጠር እና ድንጋይ ለእርሻ ገጠር ልማት ቤት ፅሕፈት እና ለኮንስትራክሽን ቤት ፅሕፈት ግልጋሎት የሚዉል ለመግዛት ስለሚፈልግ

ቁጥር ዕ/ፋ/ን/ምም/ር/01/91/17

ቀን 14/06/2017ዓ/ም

ፕሪፎርማ ማስታወቅያ

ጉዳይ፡ ለዕቃዎች ግዥ የመወዳደርያ ሃሳብ እንዲያቀርቡ ስለመጠየቅ

መስርያ ቤታችን ከዚህ ደብዳቤ ጋር ኣባሪ በተደረገው ሰንጠረዥ _ ውስጥ የተጠቀሰው በል/ሴፍትኔት በጀት አሸዋ ጠጠር እና ድንጋይ ለእርሻ ገጠር ልማት ቤት ፅሕፈት እና ለኮንስትራክሽን ቤት ፅሕፈት ግልጋሎት የሚዉል ለመግዛት ስለሚፈልግ የመወዳደርያ ሃሳብ እንድታቀርቡ ይጋብዛል፡መስርያ ቤታችን ግዥው የሚፈፅመው ብጥራትም ሆነ በዋጋ ብቁ መሆናቸው ኣረጋግጦ የመረጣቸው ሲሆን ፤ከሚፈለጉት መካከል ለከፊሎች ብቻ ዋጋ መስጠት ተቀባይነት ላያገኝ ይችላል፡፡

1. የእቃው አይነት ዝርዝር ኣባሪ በተደረገው ስንጠረዝ ላይ የመለከታል።

2. የመወዳደሪያ ሃሳቡ በታሸገ ኤንቨሎፕ ውስጥ ሆኖ እስከ 21/06/2017 ዓ/ም ለእቅድና ፋይናንስ ዕ/ት ቤት መድረስ አለበት።

3. አሸናፊ ተጫራች አሸዋ ጠጠር እና ድንጋይ ማስረከቢያ ቦታ በዋጋ መሙያ ላይ በተጠቀሰዉ ቦታ ሁኖ የማስረከቢያ ጊዜው ውል ካሰረበት ቀን ጀምሮ በ 10 ኣስር/ ቀናት ውስጥ ይሆናል፡፡

4. አቅራቢዎች ጠቅላላ ዋጋውን በቁጥርና በፊደል መፃፍ አለባቸው በቁጥርና በፊደል የተገለፀው የዋጋ መጠን መካከል አለመጣጣም ካለ በፊደል የተገለፀው ተቀባይነት ይኖረዋል። በነጠላ ዋጋ እና በጠቅላላ ዋጋ መካከል ልዩነት ካለ ነጠላ ዋጋዉ ተቀባይነት ይኖረዋል።

5. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና 12000.00 ብር አስራ ሁለት ሺ (በፊደል) በpo ወይም በጥፊ ገንዘብ በዋስትና ያልተመሰረተ የባንክ ጋራንት ከጨረታ ሰነዱ ጋር ማቅረብ አለባቸዉ ። የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ፀንቶ የሚቆይበት ጊዜ ጨረታ ከተከፈተበት ጊዜ አንስቶ ኣሸናፊ ተጫራች ውል እስኪያስር ድረስ ባሉት ቀናት ይሆናል ።

6. አቅራቢዎች በእያንዳንዱ የዕቃ ዝርዝር ማቅረቢያ ስንጠረዥ ውስጥ የእቃዉን አይነትና ብዛት ነጠላ ዋጋ እና ጠቅላላ ዋጋዉን መሙላት አንዲሁም ቀን ፊረማና የድርጅቱን ማህተም ማስፈር ይገባችዋል።

7. ለአሸናፊ ተጫራቶች አሽዋ ጠጠር ኣና ድንጋይ ሙሉ ለሙሉ በዉለታ መሰረት አጠናቆ ማስገባቱና ማጠናቀቁ ከተረጋገጠ በኅላ ቢበዛ በሰባት ቀናቶቸ ውስጥ ሙሉ ክፍያ ይከፈለዋል።

8. የመወዳደሪያ ሀሳብ ማቅረቢያ ቌንቌው በአማርኛ ነው።

9. ተጫራቶች የሚያቀርቡት ጠቅላላ ዋጋ ታክስን የሚያካትትና የማያካቲት መሆኑ መግለፅ አለበት።ታክስ ብትክክል ካልተገለጸ የቀረበዉ ዋጋ ታክስ እንዳከተተ ተቆጥሮ ዉድድሩ ይካሄዳል

10. እቃዎቹ መሟላት ያለባቸዉ መስፈርቶች (Specification) ተያይዟል፡፡

11. አሸናፊዉ አቅራቢ የሚለየዉ ለያንዳንዱ አሸዋ ጠጠር አና ድንጋይ ኣይነት (IEM BY ITEME) ዝቅተኛ ዋጋ መሰረት ይሆናል፡፡

12. ማንኛዉም ተጫራች ከጨረታ መዝግያ ቀንና ስዓት በፊት የዋጋ ማቅረብያዉ ሰነዱን (የመወዳደሪያ ሃሳብ ) ማስገባት ይኖርበታል፡፡ ከጨረታ መዝግያ ቀንና ስዓት በኋላ የቀረበ የዋጋ ማቅረቢያዉ ሰነድን የመወዳደርያ ሃሳብ ተቀባይነት የሌለዉ ሲሆን ኤንቨሎፑ ሳይከፈት ለተጫራቶች ተመላሽ እንዲሆን ይደረጋል ::

13. የመወዳደርያ ሃሳቡ ሂሳብ ዋጋ የሚቀርበዉ በኢትዮጵያ ብር ይሆናል፡፡

14. ከጨረታ ሰነድ ማስረከቢያ በፊት የቀረቡ የጨረታ ኤንቨሎፖች በሙሉ ከጨረታ መዝግያ ስዓት በኋላ ወድያዉኑ ይከፈታል።

15. የጨረታ መወዳደርያዉ በሚከተለዉ መሰረት ይሆናል የቀረቡት እቃዎች ቴክኒካል መስፈርቶችን ያሟሉ መሆናቸዉ ያረጋግጣል፣፣

16. ጨረታዉ ቴክኒክ መስፈርቱን ካሟሉት አቅራቢዎች መካከል ዝቅተኛ ዋጋ ላቀረበዉ ተጫራች አሸናፊ ይደረጋል ።

17. ተጫራች የ2017 ዓ/ም የታደሰ ያአሸዋ ጠጠር እና ድንጋይ ሕጋዊ ንግድ ፍቃድ ማቅረብ ኣለበት፡፡

18. ተጫራች የ2017 ዓ/ም የታደሰ የኣቅራቢነት ሰርቲፊኬት ማቅረብ : ኣለበት፡፡

19. ቲን ቁጥር ማቅረብ የሚችል

20. ቫት ተመዝጋቢ የሆኑና ታሕሳስ ወር ዲክለሬሽን ማቅረብ ኣለበት

21. ተወዳዳሪ አንድ ኦርጅናልና አንድ ኮፒ ለየብቻ አሽጎ ሁለቱም ፖስታዎች ባአንድ ፖስታ ዉስጥ በማሸግ ማቅረብ አለበት

NB. ፕሮፎርማ የሚዘጋበት ቀን 21/06/2017 ዓ/ም ሰዓት 8፡30 ፕሮፎርማ የሚከፈትበት ቀን 21/06/2017 ዓ/ም ሰዓት 9፡00

መመለስ
የጨረታ ምድብ