በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የተለያዩ የምግብ ነክ ዕቃዎች፣ የህንፃ መሳሪያዎች፣ የንፅህና ዕቃዎች፣ የቤትና የቢሮ ዕቃዎች፣ የኮንስትራክሽን ዕቃዎች፣ ለግብርና አገልግሎት የሚውሉ ዕቃዎች ባሉበት ሁኔታ በሃራጅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል

የሐራጅ‍‍‍‍‌‍‌‍‌‌‌‍‍‍‌‍ ጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ ማስታወቂያ

በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በህገ-ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀሱ ተይዘው የተወረሱ

  • የተለያዩ የምግብ ነክ ዕቃዎች ፣
  • የህንፃ መሳሪያዎች ፣
  • የንፅህና ዕቃዎች፣
  • የቤትና የቢሮ ዕቃዎች፣
  • የኮንስትራክሽን ዕቃዎች፣
  • ለግብርና አገልግሎት የሚውሉ ዕቃዎች ባሉበት ሁኔታ በሃራጅ ጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።

በዚህም መሰረት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች በጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ው መሳተፍ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

  1. በዘርፉ የፀና ንግድ ፍቃድ ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርቲፍኬት እና የዘመኑን ግብር የከፈለ ለመሆኑ ከግብር ሰብሳቢ መ/ቤት የተሰጠ ማስረጃ ከጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ ሰነዱ ጋር አያይዞ በጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ው ዕለት ይዞ መምጣት ይኖርበታል።
  2. ከላይ በተ/ቁ 1 በተገለፀው ተጫራቾች ማሟላት ያለባቸው መስፈርቶች ቢኖርም የመነሻ ዋጋቸው ከብር 500ሺ በታች የሆነ ማንኛውም ዕቃ ለመግዛት የሚፈልግ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርቲፊኬት ማቅረብ አይገደድም አያስፈልግም።
  3. ተጫራቾች የተዘጋጀውን የጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ ሰነድ የማይመለስ ብር 100 /አንድ መቶ ብር/ በመክፈል በመቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በውርስ መጋዘን አስተዳደር ስራ ሂደት 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 406 በአካል በመቅረብ ይህ ማስታወቂያ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ ባሉት 7 የስራ ቀናት በአካል በመቅረብ ዘወትር በስራ ሰዓት‍‍‍‍‌‍‌‍‌‌‌‍‍‍‌‍ ሰነድ መግዛት ይቻላል።
  4. ተጫራቾች የጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ ማስከበሪያ ለምግብ ነክ ዕቃዎች ብር 200,000 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) ፣ ለአልባሳት፣ ለንጽህና፣ ለኮንስትራክሽን ዕቃዎች ለእያንዳንዳቸው ብር 30,000 (ሰላሳ ሺህ) ለግብርና አገልግሎት የሚውሉ ዕቃዎችና ለቤትና ለቢሮ ዕቃዎች ለእያንዳንዳቸው ብር 6,000 (ስድስት ሺህ ) በባንክ በተረጋገጠ CPO በቅ/ጽ/ቤቱ ስም አሰርቶ ከጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ ሰነድ ጋር በጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ው ሰዓት ይዞው መቅረብ አለባቸው።
  5. ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ በጋዜጣው ከታተመበት ቀን ጀምሮ የሚቆጠር እስከ 7ተኛ ቀን ድረስ ለጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ የቀረቡ የዕቃዎች ናሙና በቅ/ፅ/ቤቱ ውርስ መጋዘን በአካል በመሄድ መመልከት ይቻላል ።
  6. ጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ው የሚካሄደው ይህ ማስታወቂያ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በሚቆጠር በ8ተኛ ቀን ሲሆን ጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ው ከጠዋቱ 4፡00 (አራት ሰዓት) ጀምሮ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በቅ/ፅ/ቤቱ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይካሄዳል።
  7. ከላይ በተራ ቁጥር 7 በተገለፀው ጋዜጣው ከታተመበት ቀን ጀምሮ የሚቆጠር በ8ተኛ የስራ ቀን ሳይሆን ሲቀር ጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ው መክፈቻ ቀን በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይሆናል።
  8. ለጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ው አሸናፊተጫራቾች ለጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ው ዋስትናያስያዙት(CPO)ከሚከፍሉት ዋጋ ጋር የሚታሰብላቸው ሲሆን፤ ለተሸናፊ ተጫራቾች ደግሞ የጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ው ውጤት ከተገለጸበት ቀን በ3 የሥራ ቀናት ውስጥ ተመላሽ ይደረግላቸዋል።
  9. የጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ው አሸናፊዎች አሸናፊ መሆናቸው በደብዳቤ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ በ5(አምስት) ቀናት ውስጥ ያሸነፈውን ዕቃ ዋጋ ገቢ በማድረግ ዕቃውን መረከብ አለበት።
  10. ከላይ በተቁ 9 በተገለጹት ቀናት ክፍያውን ገቢ ያላደረገ እና ንብረቱን ተረክበው ያልወሰዱ ተጫራቾች ለጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ ማስከበሪያ ያስያዘው ሲፒኦ ለመ/ቤቱ ገቢ ሆኖዕቃው በድጋሚ ለሽያጭ ይቀርባል፣
  11. ኮሚሽኑ የተሻለ አመራጭ ካገኘ ጨረታ‏‏‏‏‎‏‎‏‎‎‎‏‏‏‎‏ውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

አድራሻ፣

መቐለ ትራንስ ኢትዮጵያ ድርጅት ቢሮ ጎን በሚገኘው ዮሃንስ ግደይ ህንፃ ነው። ለበለጠ

መረጃ 251 34 240 7107/251 34 240 8513 በመደወል መረጃ ማግኘት ትችላላችሁ።

በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት

መመለስ
የጨረታ ምድብ
  • ሶፍትዌርና ኔትዎርክ (26)
    • ኮንስትራክሽን (301)
      • ኤሌትክትሮኒክስና ኣይሲቲ እቃዎች (553)
        • የሂሳብ ኣያያዝና ኦዲት ማድረግ (74)
          • ግብርና (198)
            • የግንባታ እቃዎች (1266)
              • ፅዳትና የንፅህና እቃዎች (234)
                • ማማከር (41)
                  • ትምህርትና ስልጠና (27)
                    • ኤሌክትሪካልና ኤሌክትሮ መካኒካል (393)
                      • ምግብና መጠጥ (175)
                        • እግድ (56)
                          • ፈርኒሽንግና ፊክስቸር (19)
                            • ፈርኒቸር (230)
                              • ጠቅላላ ስራዎች አገልግሎት (27)
                                • ስጦታዎች እና እደ-ጥበብ (2)
                                  • ጤና (41)
                                    • የቤት ዕቃዎች (44)
                                      • ኢንሹራንስ (1)
                                        • የላብራቶሪ እቃዎች እና ኬሚካል (182)
                                          • መሬትና ሊዝ (3)
                                            • ጥገና (81)
                                              • የህክምና ዕቃዎች (63)
                                                • መኣድና የተፈጥሮ ሃብት (4)
                                                  • የቢሮ እቃዎችና የፅህፈት መሳሪያዎች (268)
                                                    • ማሸግያ መጠቅለያ እና ወረቀቶች (3)
                                                      • ፎቶግራፍና ፊልም (6)
                                                        • የህትመት ስራዎች (110)
                                                          • የማስታወቅያ ስራዎች (11)
                                                            • ኪራይ (213)
                                                              • ሽያጭ (333)
                                                                • የጥበቃ ስራዎችና ሰኪዩሪቲ (40)
                                                                  • የተሽከርካሪ መለዋወጫ እቃዎች (627)
                                                                    • የስፖርትና ትጥቅና ተዛማጅ እቃዎች (44)
                                                                      • ቴሌኮምኒኬሽን እቃዎች (13)
                                                                        • ጨርቃ ጨርቅና የቆዳ ውጤቶች (286)
                                                                          • የትራንዚትና መጓጓዠያ ኣገልግሎት (100)
                                                                            • የተሽከርካሪና ከባደ ማሽነሪ (166)
                                                                              • መጋዝን (25)
                                                                                • እንጨት እና የእንጨት ስራ (76)
                                                                                  • ኣልሙኒየም፡ መስትዋትና የብረታ ብረት ስራዎች (88)
                                                                                    s