የኢትዮጵያ ልማት ባንክ መቐለ ዲስትሪክት ለአቶ አታኽልቲ ሐጎስ ዝዝጊ ለሰጠው ብድር አመላለስ በዋስትና የያዘውንና ከዚህ በታች ባለው ሰንጠረዥ የተመለከተውን ንብረት በአዋጅ ቁጥር 97/90፣ 216/92 እና 1147/11 በተሰጠው ስልጣን መሠረት በሐራጅ ለመሸጥ ይፈልጋል::
  • የተለቀቀበት ቀን: ሰኞ ሐምሌ 15, 2016 ( ከ 2 ወር)
  • መዝግያ ቀን: ሓሙስ ነሐሴ 9, 2016 05:00 ጥዋት (ተዘጋ)
  • የጨረታ ማስከበርያ ዋጋ:25%
  • ቦታ: ኣክሱም
  • የጨረታ ደኩመንት ዋጋ:
  • ጨረታ ሚከፈትበት ቀንና ሰዓት: ሓሙስ ነሐሴ 9, 2016 07:00 ከሰአት
  • ናይ ገዛ/ህንፃ ሓራጅ/
  • Print
  • Pdf

የሐራጅ ማስታወቂያ

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ መቐለ ዲስትሪክት ለአቶ አታኽልቲ ሐጎስ ዝዝጊ ለሰጠው ብድር አመላለስ በዋስትና የያዘውንና ከዚህ በታች ባለው ሰንጠረዥ የተመለከተውን ንብረት በአዋጅ ቁጥር 97/90፣ 216/92 እና 1147/11 በተሰጠው ስልጣን መሠረት በሐራጅ ለመሸጥ ይፈልጋል::

የተበዳሪው/ መያዣ ሰጪው ሰምየመያዣ ንብረቱ አድራሻለሐራጅ የቀረበ ንብረት ዓይነትና ዝርዝርየቦታው ስፋት በካሜየሐራጁ መነሻ ዋጋ / በብር/የሐራጁ ደረጃሐራጅ የሚካሄድበት እና ሰ
አታኽልቲ ሓጎስ ዝዝጊበትግራይ ክልል ማዕከላዊ ዞን አከሱም ከተማ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ቁጥር 7299/ድ/2016 የሆነየሆቴል ድርጅት ህንፃዎች እና የሆቴል መገልገያ ቁሳቁሶች4552.7427,806,388.86 lug ሰባት ሚሊዮን ስምንት መቶ ስድስት ሺህ ሦስት መቶ ሰማንየ ስምንት ብር 186 ሣንቲም/ሁለተኛጎሃሌ 09 ቀን 2016 ዓ/ም ከጧቱ 5:00-7:00

ማሳሰቢያ

1. ተጫራቾች ንብረቱን ለመጎብኘት ከፈለጉ አሰቀድሞ ከባንኩ ጋር ቀጠሮ በመያዝ ከሐራጁ ቀን በፊት ንብረቱን መጎብኘት ይችላሉ።

2. ተጫራቾች የሐራጁን መነሻ ዋጋ 25% (ሀያ አምስት በመቶ) በባንክ ማርኛ ሲፒኦ (CPO) ብቻ እሰርተው ከሐራጁ ቀን በፊት ማስያዝ ወይም ሐራጁ በሚካሄድበት ዕለት ሐራጁ ከመከፈቱ በፊት ይዘው መቅረብ ይኖርባቸዋል። በሐራጁ የተሸነፉ ተጫራቾች ያስያዙት ሲፒኦ (CPO) ወዲያውኑ ይመለስላቸዋል።

3. በሐራጁ ለመሳተፍ የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች ሐራጁ ከመጀመሩ በፊት ከጠዋቱ 5፡00 ሰዓት በፊት ባለው ጊዜ ሐራጁ በሚካሄድበት ቦታ በአካል ወይም በህጋዊ ወኪል በኩል ቀርቦ መመዝገብ ይኖርበታል።

4. ሐራጁ ከላይ በተገለፀው ቀንና ስዓት ተበዳሪው/መያዣ ሰጪው ወይም ህጋዊ ወኪላቸው፣ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸውና ታዛቢዎች በተገኙበት በፕሮጀክቱ ቅጥር ግቢ ውስጥ ይካሄዳል፡፡ በጨረታ 'ንና ሰዓት መያዣ ሰው ወይም ህጋዊ ወኪላቸው እና ታዛቢዎች ባይገኙም ሐራጁ ይካሄዳል።

5. በሐራጁ የተሻለ ዋጋ ያቀረበ ተጫራች ማሸነፉን የሚገልፅ ደብዳቤ ከባንኩ ሊደርሰው አሸናፊ ይሆናል።

6. ሐራጁን ያሸነፈ ተጫራች አሸናፊ መሆኑ በፅሁፍ ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ ያሸነፈበትን ዋና በ15 ተከታታይ ቀናት ጊዜ ውስጥ ለባንኩ አጠቃሎ ገቢ ማድረግ ይኖርበታል። በተገለፀው ጊዜ ውስጥ አሸናፊው ገንዘቡን ገቢ ካላደረገ ሐራጁ ይሰረዛል፣ ያስያዘው ገንዘብም ለባንኩ ገቢ ይሆናል፡፡ ሐራጁ ያሸነፈ ተጫራች ያሸነፈበትን ገንዘብ በጥሬ ለባንኩ መክፈል ይኖርበታል። ሆኖም አሸናፊው በባንኩ የብድር ፖሊሲ መሠረት አስፈላጊውን መስፈርቶች ካሟላና የፕሮጀክቱን ስራ የሚያስቀጥል ከሆነ ንብረቱን የከፊል ብድር ለመግዛት መጠየቅ ይችላል።

7 የጉምሩክ ቀረጥና ታክስ ያልተከፈለባቸው ተሽከርካሪ እና ማሽነሪዎች በተመለከተ ገዢው የቀረጥ ነፃ መብት ሊኖረው ይገባል ወይም በንብረቶቹ ላይ በመንግስት የሚፈለገውን ቀረጥና ታክስ መክፈል ይኖርበታል።

8. የንብረቱ ስመ ንብረት ለገዢው እንዲዞር ባንኩ ለሚመለከተው መንግስታዊ አካል ደብዳቤ ይፅፋል፡፡ ገዢው ጉዳዩን ተከታትሎ ያስፈፅማል።

9. ሐራዱ ከመካሄዱ በፊትም ሆነ ከተካሄደ በኋላ ባንኩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ወይም ብድሩ ከተከፈለ ሐራጁ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

10. ሐራጁ ያሸነፈ ተጫራች የሽያጩን 15% ተጨማሪ እሴት ታክስ እና ሌሎች ገዥ እንዲከፍላቸው በሕግ የተወሰኑ ክፍያዎች፣ የስም ማዛወሪያ ክፍያን ጨምሮ ይከፍላል።

11. ለተጨማሪ መረጃ መቐለ ዲስትሪክት ሎን ዎርክአውት ዲቪዥን በኣካል በመቅረብ ወይም በስልክ ቁጥር 0344407439 ፣ 0344419016 ማግኘት ይችላሉ፡፡

መመለስ
የጨረታ ምድብ