የኢትዩጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የልማትና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን የትግራይ ኣህጉር ስብከት ልማት ማስተባበሪያ ፅህፈት ብኣዉነ መርሃ የገጠር ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት በእንደርታ ወረዳ ለሚያካሂደዉ የት/ቤት ኣቅም ግንባታ ስራ ኣጎልግሎት የሚዉሉ የቤተ ንባብ ሸልፎች ጠረፔዛዎችና ወምበሮች ለማሳራት ይፈልጋል በዚህ መሰረት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾችን ይፈልጋል፡፡
  • የተለቀቀበት ቀን: ዓርቢ መስከረም 8, 2013 (ከ 4 ዓመታት)
  • መዝግያ ቀን: ዓርቢ መስከረም 15, 2013 04:00 ጥዋት (ተዘጋ)
  • የጨረታ ማስከበርያ ዋጋ:2000.00
  • ቦታ: መቐለ
  • የጨረታ ደኩመንት ዋጋ:20.00
  • ጨረታ ሚከፈትበት ቀንና ሰዓት: ዓርቢ መስከረም 15, 2013 04:30 ጥዋት
  • ዕንፀይቲን ስራሕቲ ዕንፀይቲ/
  • Print
  • Pdf

1 የኣቅራቢነት ህጋዊ ፍቃድ ያላቸው።

2 የ2012/2013 ዓ/ም ግብር የከፈሉና የዓመት ንግድ ፍቃድ ያሳደሱ::

3 ተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይ የሆኑና ያለፈዉ ወር ተ.እ.ታ የከፈሉበት መረጃ ማቅረብ የሚችሉ::

4 ተጫራቾች ከተራ ቁጥር 1-3 የተጠቀሱት መረጃዎች ኦርጂናል በመያዝ የጨረታ ሰነድ መውሰድ አለባቸው፡፡፡

5 ተጫራቾች የጨረታዉን ሰነድ የማይመለስ 20.00 / ሃያ ብር/ በመግዛት ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ 10 / አስር / ቀናት ዉስጥ የጨረታ ሰነድ መግዛት ይችላሉ::

6 የጨረታ ማስከበሪያ ብር 2000 /ሁለት ሺ ብር / የባንክ ዋስትና ወይም CPO በተለየ ፖስታ ኣሽገው ወይም በኣካል ይዘው መቅረብ የሚችሉ::

7 ዕቃው ውል ከተፈፀመበት ቀን ጀምሮ በ20 ተከታታይ ውስጥ እቃውን ፕሮጀክቱ በሚያዘው ባለሙያ ስለ ትክክለኛነቱ በማረጋገጥ ፅ/ቤታችን ማቅረብ የሚችል፤

8 ተሞልቶ የሚቀርበዉ ሰነድ በተሰጠው ስፔስፊኬሽን መሰረት ሆኖ ስርዝ ድልዝ የሌለበትና መሆን ኣለበት፤

9 የጨረታዉ ሰነድ ዋናዉና ቅጂ ለየብቻዉ በስም በታሸገ ኢንቨሎፕ ለጨረታዉ በተዘጋጀ ሳጥን ማስገባት ያስፈልጋል::

10 የጨረታዉ ሳጥን በ 15/01/2013ዓ/ም ጥዋት 4:00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ዕለት ከጥዋቱ 4:30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት ወይም መገኘት የማይችሉ ከሆነ ሰነዳቸዉን በማሟለት በፖስታቸዉ ላይ ይከፈትልኝ ብለዉ ከፈረሙና የድርጅቱ ማህተም ካደረጉ በሌሉበት በትግራይ አህጉረ ስብከት ልማት ማስተባበሪያ ፅ /ቤት ይክፈታል::

11 ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታዉን በሙሉ ወይም በክፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ::

አድራሻ 05 ቀበሌ ኮንደሚኒየም አጠገብ የኦርቶዶክስ የህፃናት ማሳደጊያ ድርጅት

ለበለጠ መረጃ 03 44 40 97 51 /03 44 40 97 52

መመለስ
የጨረታ ምድብ