የጨረታ ማስታወቂያ
የሰሜን ሪጅን የመ/ሠ/ማ/ዋ/አስተዳደር ጽ/ቤት ለ2018 ዓ/ም በጀት ዓመት ለሪጅኑ አገልግሎት የሚውሉ ንብረቶችን ለምሳሌ ተሽከርካሪ ወንበር፣ አግድም ወንበር፣ የፕሪንተር ቀለም ፣ የተለያዩ ወንበሮች፣ የመኪና ጎማ፣ የመኪና ባትሪ፣ ጫማ፣ የሞተር ዘይት፣ የጽዳት ዕቃዎች፣ የስቴሽነሪ /የጽህፈት መሳሪያዎች/ ዕቃዎችን አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
በዚሁ መሰረት ተጫራቾች፡-
1. የዘመኑ የታደሰ ህጋዊ ፈቃድ ያላችሁ የንግድ ፈቃዱ ኮፒ መያያዝ አለበት፣ የዘመኑ የአቅራቢነት የምስክር ወረቀት ያላቸው፣ የዘመኑ የቫት ተመዝጋቢ የሆኑና ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፣ የዘመኑ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) ሰርተፊኬት ኮፒ መያያዝ አለበት፣
2. ተጫራቾች የጨረታ ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 16ኛው ቀን ድረስ የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።
3. ተጫራቾች ለተፈላጊ አቅርቦቶች የጨረታ ማስከበሪያ ለእያንዳንዱ ሎት 10,000 (አስር ሺህ ብር) ዋስትና በባንከ የተረጋገጠ ሲፒኦ የጨረታ ሳጥን ከመክፈቱ በፊት ማስያዝ አለባቸው።
4. እንዲሁም ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ሰነዱን ከግዥ ክፍል በመግዛት ለተከታታይ 16ቀን የሚቆይ ሲሆን ጨረታው በመጨረሻው ቀን 4፡00 ተዘግቶ 4፡30 ህጋዊ ወኪሎች ባሉበት ይከፈታል። 16ኛው ቀን የእረፍት ወይም የበዓል ቀን ከሆነ ጨረታው ከላይ በተገለፀው ሰዓት በቀጣይ የስራ ቀን ይከፈታል።
5. ለማንኛውም ዕቃ ናሙና ማቅረብ ግዴታ ነው፡፡
6. አስተዳደሩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ስቁ. 034 241 8068 / 034 241 5758
ሰሜን ሪጅን የመንግስት ሠራተኛ ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር ጽ/ቤት