Tigray Agriculture and Rural Development Bureau

አነስተኛ ዋጋ ላላቸው የዋጋ ማቅረቢያ ግዥ መፈፀሚያ

(Request for Quotation)

የጨረታ ሰነድ

ለግንባታ ስራዎች

Maintenance of the Existing Regional Plant Health Clinic Office

ET-DRDIP 2-2018-RPCU04-CW-RFQ

ጉዳዩ፦ ለግንባታ ስራዎች ግዥ የመወዳደሪያ ሀሳብ እንዲያቀርቡ ስለመጠየቅ፣

መስሪያ ቤታችን ከዚህ ደብዳቤ ጋር አባሪ በተደረገው ሠንጠረዥ ውስጥ በተጠቀሰው ዝርዝር መሰረት የግንባታ ስራዎችን ግዢ መፈፀም ስለሚፈልግ ግዢውን የሚፈፀመው ከታች የተዘረዘሩትን ሁኔታዎች ከሚያሟሉት መካከል ዝቅተኛ ዋጋ ካቀረቡት ተጫራቾች ጋር ነው፡፡

1. የተፈላጊ የግንባታ ስራዎች ዝርዝር አባሪ በተደረገው ሠንጠረዥ ላይ ተመልክቷል ።

2. የመወዳደሪያ ሃሳቡ በታሸገ ኢንቨሎፕ ውስጥ ሆኖ እስከ 27/04/2018 ዓ.ም 3፡30 ሰዓት ለግዢ ፈጻሚው መስሪያ ቤት ቢሮ ቁጥር 12 መድረስ አለበት፡፡የመወዳደሪያ ሃሳቡ በ 27/04/2018 ዓ.ም ሰዓት 4፡00 ይከፈታል።

3. ጠቅላላ የግንባታ ስራ ዋጋው በቁጥርና በፊደል መጻፍ አለባቸው :: በቁጥርና በፊደል በተገለፀው የዋጋ መጠን መካከል አለመጣጣም ካለ በፊደል የተገለፀው ተቀባይነት ይኖረዋል :: በነጠላ ዋጋ እና በጠቅላላ ዋጋ መካከል ልዩነት ካለ ነጠላ ዋጋው ተቀባይነት ይኖረዋል ።

4. የቀረበው የግንባታ ስራ ግዢ መወዳደሪያ ጨረታው ከተከፈተበት ዕለት ጀምሮ በ 45 ቀናት ውስጥ ሲሆን ስራው የሚጠናቀቀው የሥራ ትዕዛዝ ከተሰጠበት ዕለት ጀምሮ በሚቆጠር 45 ቀናት ይሆናል ።

5. የቀረበው የግንባታ ስራ ግዢ መወዳደሪያ ጨረታው ከተከፈተበት ዕለት አንስቶ ለ 20 ቀናት ፀንቶ ይቆያል ::

6. አሸናፊ ተጫራቶች የግንባታ ስራ ሙሉ ለሙሉ በውለታ መሰረት አጠናቀቃቸው ከተረጋገጠ በኋላ ቢበዛ 15 ቀናት ውስጥ ሙሉ ክፍያ ይከፈለዋል " ለግንባታ ስራ እንደ አስፈላግነቱ እየታየ ለተሰራው ስራ ብቻ ክፍያ መፈፀም የሚቻልበት ሁኔታ ሊታይ ይችላል ፡፡

7. የመወዳደሪያ ሀሳብ ማቅረቢያ ቋንቋው በአማርኛ ነው ።

8. ተጫራቶች የሚያቀርበት ጠቅላላ ዋጋ ታክስን የሚያካትትና የማያካትት መሆኑ መግለጽ አለበት ። ታክስ በትክክል ካልተገለፀ የቀረበው ታክስ እንዳካተተ ተቆጥሮ ውድድሩ ይካሄዳል :

9. የግንባተ ስራ መሟላት ያለባቸው መስፈርቶች /Design, Bill of Quantity and drawings / ተያይዟል ::

10. ተጫራቾች የሚያቀርቡት የመወዳደሪያ ሀሳብና ዋጋ ፊርማቸውን ፣ ቀንና የድርጅቱን ማህተም ማስፈር ኣለበት ።

11. ማንኛውም ተጫራች ከጨረታ መዝጊያ ቀንና ሰዓት በፊት የዋጋ ማቅረቢያው ሰነዱ / የመወዳደሪያ ሃሳብ/ ማስገባት ይኖርበታል :: ከጨረታ መዝጊያ ቀንና ሰዓት በኋላ የቀረበ የዋጋ ማቅረቢያ ሰነድ የመወዳደሪያ ሃሳብ ተቀባይነት የሌለው ሲሆን ኤንቨሎፑ ሳይከፈት ለተጫራቶች ተመላሽ እንዲሆን ይደረጋል ።

12. የመወዳደሪያ ሂሳቡ ዋጋ የሚቀርበው በኢትዮጵያ ብር ይሆናል ::

13. ከጨረታ ሰነድ ማስረከቢያ ሰዓት በፊት የቀረቡ የጨረታ ኤንቨሎፖች በሙሉ ከጨረታ መዝጊያው ሰዓት በኋላ ወዲያውን ይከፈታሉ ።

14. በጨረታው መሳተፍ የሚትችሉት በግንባታ ስራው ቢያንስ አንድ እና ከዚያ በላይ ተመሳሳይ ስራ የሰሩ መሆን አለባቸው ::

15. የክፍያ ሁኔታ በየግንባታው ደረጃ እየታየ የሚከፈልበት ሁኔታ ለተጠናቀቀው ስራ በባለሙያና በኃፊ እየተረጋገጠ መከፈል እንዳለበት በስምምነት ላይ ሊደረስ ይችላል ::

16. የጨረታ ማወዳደሪያው በሚከተለው መሰረት ይሆናል :

• በጨረታ ሰነዱ ላይ በተገለፁት BoQ Specification ና Drawing በትክክል ሰርቶ በግዜው ማስረክብ የሚችል፡

• በቀረበው ዋጋ ላይ የሂሳብ ድምር ስህተት ካለ እንዲታረም ይደረጋል ። ውድድሩ የሚካሄደው እና ዝቅተኛ ዋጋ አቅራቢው የሚለየው በታረመው ዋጋ መሰረት ይሆናል ።

17. ጨረታው የቴክኒክ መስፈቱን ካሟሉት አቅራቢዎች መካከል ዝቅተኛ ዋጋ ላቀረበው ተጫራች አሸናፊው ይደረጋል ።

18. ተጫራቶች የሚከተሉት ሰነዶች ከጨረታ ሰነዱ ጋር ማያያዥ ይኖርባቸዋል ::

➢ የታደሰ ንግድ ፍቃድ የ 2018 ዓ/ም ኮፒ

➢ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ኮፒ

➢ የቫት ምዝገባ ሰርትፊኬት ና የጥቅምት 2018 ዓ/ም ሻት ዲክላሬሽን ኮፒ

➢ የታደሰ ደረጃ ስምንት( Grade 8 GC/BC) እና ከዝያ በላይ የኮንስትራክሽን የስራ ፍቃድ ኮፒ

19. መስሪያ ቤታችን የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታው በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው ።

የጨረታ ሰነዱ (BoQ Specification, Drawing) ከቢሯችን ቢሮ ቁጥር 12 የግዥ ቡድን መውሰድ ይኖርባቸዋል።