⚡ AI Quick Summary
* ተጫራቾች በዘርፉ የፀና ንግድ ፈቃድ፣ የግብር ከፋይ መለያ (TIN)፣ የግብር ክሊራንስ እና 5% የጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ (CPO) ማቅረብ የሚኖርባቸው ሲሆን፣ ግምታቸው ከ500,000 ብር በላይ ለሆኑ ዕቃዎች የVAT ምዝገባ ሰርቲፊኬት ማቅረብ ግዴታ ነው።
* የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ 100 ብር በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000012078537 ገቢ በማድረግ ከጽሕፈት ቤቱ ቢሮ ቁጥር 104/411 በአካል በመቅረብ መግዛት ይቻላል።
* ተጫራቾች ዕቃዎቹን ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 7 ቀናት ውስጥ መመልከት የሚችሉ ሲሆን፣ ጨረታው በ8ኛው ቀን ከቀኑ 7:30 ተዘግቶ በ7:45 ይከፈታል።
* የጨረታው አሸናፊ ማሸነፉ ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ በ5 ቀናት ውስጥ ሙሉ ክፍያ ፈጽሞ ዕቃዎቹን መረከብ አለበት።
የዕቃዎች ጨረታ ሽያጭ ማስታወቂያ
ማስታወቂያ ቁጥር 2/2019
በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ተወርሰው የሚገኙ የተለያዩ የንጽህና መጠበቂያ እና የኮስመቲክስ ዕቃዎች ፣ የእህል ምርት ውጤቶች ሌሎች ልዩ ልዩ ዕቃዎች ባሉበት ሁኔታ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሽጥ ይፈልጋል።
1) በመሆኑ ቅ/ጽ/ቤቱ ባወጣው የዕቃ ሽያጭ መወዳደር የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የጨረታ መስፈርቶች የሚያማሉ ተጫራቾች በጨረታው መሳተፍ የሚችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
ሀ) በዘርፉ የፀና ንግድ ፍቃድ ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር፡ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርቲፍኬት እና የዘመኑን ግብር የከፈለ ለመሆኑ ከግብር ሰብሳቢ መ/ቤት የተሰጠ የምስክር ወረቀት /ክሊራንስ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዞ በፖስታ በማሽግ ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖሩበታል።
ለ) የዚህ አንቀጽ ፊደል ተራ (ሀ) ድንጋጌ ቢኖሩም ግምታዊ ዋጋ ከብር 500ሺ በታች የሆነ ማንኛውም ዕቃ ለመግዛት የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርቲፊኬት ማቅረብ አያስፈልግም።
2. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱ ዘወትር በስራ ሰዓት ከሰኞ እስከ ዓርብ እና ቅዳሜ ከ2፡00 ሰዓት እስከ 6፡00 ሰዓት የማይመለስ ብር 100/አንድ መቶ ብር/ በኢትዮጵያ ንግድ በሒሳብ ቁጥር 1000012078537 በመክፈል ደረሰኝ ከጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 104 እንዲሁም የጨረታ ሰነድ ቢሮ ቁጥር 411 በመምጣት ይህ ማስታወቂያ አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ እስከ መዝጊያ ቀን ድረስ ዘወትር በስራ ሰዓት በአካል በመሄድ ሰነዱ መግዛት ይቻላል።
3. ተጫራቾች ማስታወቂያ በጋዜጣው ከታተመበት ቀን ጀምሮ የሚቆጠር አስከ 7ተኛ ቀን ድረስ ለጨረታ የቀረቡ ዕቃዎች ናሙና በጽ/ቤቱ በሚገኙ መጋዘኖች መመልከት ይችላሉ።
4. ጨረታው የሚካሄደው ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የሚቆጠር በ8ተኛው ቀን ሲሆን ጨረታው ከቀኑ 7፡30 (ሰባት ሰአት ከሰላሳ ዲቂቃ) ተዘግቶ 7፡45 (ሰባት ሰኣት ከአርባ አምስት ደቂቃ) ይከፈታል።
5. ከላይ በተራ ቁጥር 4 ላይ በተገለፀው ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የሚቆጠር 8ተኛው ቀን የሥራ ቀን ሳይሆን ሲቀር ጨረታው መዝጊያና መክፈቻ ቀን በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይሆናል።
6. ተጫራቾች በግልጽ ጨረታ ለሚወዳደርባቸው ዕቃዎች የሰጡትን ዋጋ አምስት በመቶ(5%) የጨረታ ማስከበሪያ በቅ/ጽ/ቤቱ ስም ETHIOPIA customs commission mekelle branch office በሚል በባንክ አሰርተው ማስያዝ ይጠበቅባችል።
7. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በቅ/ፅ/ቤቱ የመሰብሳብያ አደራሽ 4ተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 401 ይካሄዳል።
8. ተጫራቾች ያስያዙት የጨረታ ዋስትና የጨረታ ውጤት በተገለጸው በ3 (ሰሶት) ቀናት ውስጥ ተመላሽ ይደረግላችዋል።
9. የጨረታው አሸናፊ ጨረታውን ለማሸነፉ ከተገለጸለት ጊዜ ጀምሮ 5(አምስት) ቀናት ውስጥ ያሸነፈበት ዕቃ ዋጋ ገቢ በማድረግ ዕቃውን መረከብ አለበት።
10. ከላይ በተ/ቁ 9 በተገለጹት ቀናት ውስጥ ክፍያውን ገቢ ያላደረጉ እና ንብረቱን ተረክበው ያልወሰዱ ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት ዋስትና ለቅ/ጽ/ቤቱ ገቢ ሆኖ ዕቃው በድጋሜ ለሽያጭ የሚቀርብ ሲሆን ነገር ግን የዕቃው ዋጋ ገቢ አድርጎ ዕቃው በሁለት ወር ውስጥ ካልወጣ ለንብረቱ የተከፈለው ዋጋ ለመስሪያቤቱ ገቢ ሆኖ እቃው እንደተተወ ተቆጥሮ በሽያጭ ይወገዳል።
11. በጨረታ የሚሸጠው በተቋሙ ከመወረሱ በፊት የዕቃዉ አስመጪ ፤ ወኪል፤ባለቤት ወይም ቤተሰብ በማንኛውም መልኩ በጨረታ መሳተፍ አይችልም።
12. ቅ/ፅ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ ሊሰርዝ ይችላል፡፡ ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር ኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት +251342407107 ወይም +251342408513/ በመደወል ተጨማሪ መረጃ ማግኘት የምትችሉ መሆኑ እንገልፃለን።
በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት