Gomerk Commision Mekelle Branch Office

የዕቃዎች ጨረታ ሽያጭ

ማስታወቂያ ቁጥር 14/2018

በኢትዮጵያ ጉምሩከ ኮሚሽን መቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት እና በስሩ የሚገኙ መጣቢያዎች ተይዘው እና ተወርሰው የሚገኙ የተለያዩ አዳዲስ ጨርቃ ጨርቅ ፣ የተሽከርካሪ መለዋወጫ ዕቃዎች፣ የህንፃ መሳሪያ ዕቃዎች እና የምግብ ነክ ዕቃዎች እንዲሁም ሌሎች ዕቃዎች ባሉበት ሁኔታ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሽጥ ይፈልጋል።

1) በመሆኑ ቅ/ጽ/ቤቱ ባወጣው የዕቃ ሽያጭ መወዳደር የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የጨረታ መስፈርቶች የሚያማሉ ተጫራቾች በጨረታው መሳተፍ የሚችሉ መሆኑን እንገልፃለን።

ሀ) በዘርፉ የፀና ንግድ ፍቃድ ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርተፍኬት እና የዘመኑን ግብር የከፈለ ለመሆኑ ከግብር ሰብሳቢ መ/ቤት የተሰጠ የምስክር ወረቀት /ክሊራንስ/ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዞ በፖስታ በማሽግ ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርበታል።

ለ) የዚህ አንቀጽ ፊደል ተራ (ሀ) ድንጋጌ ቢኖሩም ግምታዊ ዋጋ ከብር 500 ሺህ በታች የሆነ ማንኛውም ዕቃ ለመግዛት የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርተፊኬት ማቅረብ አያስፈልግም።

2. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ዘወትር በስራ ሰዓት ከሰኞ እስከ ዓርብ እና ቅዳሜ ከ2፡00 ሰዓት እስከ 6፡00 ሰዓት የማይመለስ ብር 100/አንድ መቶ ብር/ በኢትዮጵያ ንግድ በሒሳብ ቁጥር 1000012078537 በመክፈል ደረሰኝ ከጉምሩክ ኮሚሽን መቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 104 እንዲሁም የጨረታ ስነድ ቢሮ ቁጥር 411 በመምጣት ይህ ማስታወቂያ አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ እስከ መዝጊያ ቀን ድረስ ዘወትር በስራ ሰዓት በአካል በመሄድ ሰነዱን መግዛት ይቻላል።

3. ተጫራቾች ማስታወቂያው በጋዜጣው ከታተመበት ቀን ጀምሮ የሚቆጠር እስከ 5ተኛ ቀን ድረስ ለጨረታ የቀረቡ ዕቃዎች ናሙና በጽ/ቤቱ እና በመጣቢያዎች የሚገኙ መጋዘኖቻችን በአካል እየሄዱ መመልከት ይችላሉ።

4. ጨረታው የሚካሄደው ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የሚቆጠር በ6ተኛው ቀን ሲሆን ጨረታው ከቀኑ 7፡30 (ሰባት ሰዓት ከሰላሳ ደቂቃ ) ተዘግቶ 7፡45 ( ሰባት ሰዓት ከአርባ አምስት ደቂቃ ) ይከፈታል።

5. ከላይ በተራ ቁጥር 4 ላይ በተገለፀው ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የሚቆጠር 6ተኛው ቀን የሥራ ቀን ሳይሆን ቢቀር የጨረታው መዝጊያና መክፈቻ ቀን በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይሆናል።

6. ተጫራቾች በግልጽ ጨረታ ለሚወዳደርባቸው ዕቃዎች የሰጡትን ዋጋ አምስት በመቶ(5%) የጨረታማስከበሪያ በቅ/ጽ/ቤቱ ስም ETHOPIA customs commission mekelle branch office በሚል በባንክ አሰርተው ማስያዝ ይጠበቅባችኋል።

7. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በቅ/ፅ/ቤቱ የመሰብሰቢያ አዳራሽ 4ተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 401 ይካሄዳል።

8.ተጫራቾች ያስያዙት የጨረታ ዋስትና የጨረታ ውጤት በተገለጸው በ3 (በሶስት) ቀናት ውስጥ ተመላሽ ይደረግላጨቸዋል።

9. የጨረታው አሸናፊ ጨረታውን ለማሸነፉ ከተገለጸለት ጊዜ ጀምሮ 5(አምስት) ቀናት ውስጥ ያሸነፈበት ዕቃ ዋጋ ገቢ በማድረግ ዕቃውን መረከብ አለበት።

10. ከላይ በተ/ቁ 9 በተገለጹት ቀናት ውስጥ ክፍያውን ገቢ ያላደረጉ እና ንብረቱን ተረክበው ያልወሰዱ ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት ዋስትና ለቅ/ጽ/ቤቱ ገቢ ሆኖ ዕቃው በድጋሚ ለሽያጭ የሚቀርብ ሲሆን ነገር ግን የዕቃው ዋጋ ገቢ አድርጎ ዕቃው በሁለት ወር ውስጥ ካልወጣ ለንብረቱ የተከፈለው ዋጋ ለመስሪያ ቤቱ ገቢ ሆኖ እቃው እንደተተወ ተቆጥሮ በሽያጭ ይወገዳል።

11. በጨረታ የሚሸጠው በተቋሙ ከመወረሱ በፊት የዕቃዉ አስመጪ ፤ ወኪል፤ባለቤት ወይም ቤተሰብ በማንኛውም መልኩ በጨረታ መሳተፍ አይችልም።

12. ቅ/ፅ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ ሊሰርዝ ይችላል።

ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር፡- +251342407107 ወይም +251342408513/ በመደወል ተጨማሪ መረጃ ማግኘት የምትችሱ መሆኑን እንገልፃለን።