Ethio Telecom

ቀን 04/10/2018

የጨረታ ቁጥር ሰሪ 4285575

የፅዳት አገልግሎት የማዕቀፍ ዉል ግዥ ግልጽ ጨረታ

ኢትዮ ቴሌኮም ሰሜን ሪጅን በሪጅኑ ለሚገኙ የቢሮ እና የኣገልግሎት ማእከል የተለያዩ ቦታዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ የፅዳት አገልግሎት ስራ ማሰራት ስለሚፈልግ በዘርፉ ንግድ ፍቃድ ያላችሁ አቅራቢዎች እንድትወዳደሩ ይጋብዛል፡፡

I. ተጫራቾች ማሟላት የሚገባቸው መስፈርቶች

1. በዘርፉ የዘመኑ የታደሰ ንግድ ፍቃድ፣የግብር ከፋይ መለያ ሰርተፍኬት፣ ቫት ምዝገባ ሰርተፍኬት እና የታክስ ክሊራንስ ምስክር ወረቀት ማቅረብ አለባቸው ::

II. ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነድ ሲያዘጋጁና ሲያቀርቡ የግድ ሊያሟላቸዉ የሚገቡ ደንቦች

1. ሪጅኑ በሁለት ጊዜ ጨረታ አከፋፈት /Two Envelop bidding/ ደንብን ስለሚከተል በመጀመሪያ ቴክኒከል ዋናዉና ቅጁ /Technical original and copy/ ለብቻዉ የሒሳብ መዝገብ ሪፖርት፣የስራ ልምድ / Testimonial letter / ፣ የሰዉ ሀይል እና የማቴሪያል አቅርቦት ዝርዝር መግለጫና ከላይ በተ.ቁ 1. ንኡስ ቁጥር 1 የተገለጹትን መሰፈርቶች ጨምሮ ማቅረብ አለበት፡፡

܀ ዋጋ በቴክኒከል መጫረቻ ሰነድ/ Technical proposal/ላይ አይገለፅም፡፡

2. በዋጋ መወዳደሪያ /commercial offer/ ላይ ዋጋን በተመለከተ ዋናዉና ቅጁ /orignal and copy/ ለብቻዉ የአንድ ዋጋ ለኣንድ ካሬ ሜትር ማቅረብ ይኖርበታል፡፡

3. ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ብር 50,000.00 /ሃምሳ ሺ/ ሲፒኦ በቴክኒከል መጫረቻ ሰነድ ውስጥ ወይም ለብቻው ጨረታው በሚከፈትበት ሰአት የግድ ማቅረብ አለባቸው ::

4. ተጫራቾች ሰሜን ሪጅን ኢትዮ ቴሌኮም ፣3ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 301 በመምጣት የማይመለስ ብር 200 በመክፈል ከሰኔ 04 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለዚህ ጨረታ ተብሎ የተዘጋጀዉን

5. የጨረታ ሰነድ መዉሰድ ይችላሉ ፡ የመጫረቻ ሰነዳቸዉን አዘጋጅተዉ እስከ ሰኔ 19 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ሰዓት ድረስ በተዘጋጀዉ የጨረታ ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል ፡፡ ከቀኑ 8:00 ሰዓት በኋላ የሚቀርብ ሰነድ ተቀባይነት የለዉም ፡፡

5. ጨረታዉ እስከሚዘጋበት ቀንና ሰዓት ድረስ ገቢ የተደረጉ የመጫረቻ ሰነድ ፍላጎቱ ያላቸዉ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ኢትዮ ቴሌኮም 5ኛ ፎቅ በሚገኘዉ የስብሰባ አዳራሽ ሰኔ 19 ቀን ፣2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡15 ይከፈታል ፡፡

6. መ/ቤቱ ጨረታዉን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ በሕግ የተጠበቀ ነዉ፡፡

አድራሻ የሰሜን ሪጅን ኢትዮ ቴሌኮም መቐለ

ስ.ቁ. 0344-40-20-20