Ethiopian Electric Utility (EEU) Shire Region Office

ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ

ጨረታ ቁጥር SREU/SC-003/2018

የሽረ ሪጅን ኤሌክትሪክ አገልግሎት በትግራይ ክልል የሚገኙ ትልልቅ ከተሞች ላይ መደበኛ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችሉ ቀላል የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች (አውቶሞቢል እና ዳብል ካብ ፒክአፕ) በግልፅ ጨረታ ለአንድ ዓመት የሚቆይ በኪራይ አወዳድሮ መከራየት ይፈልጋል።

ዝርዝሩም እንደሚከተስው ይሆናል፡-

ጨረታው ቁጥር

ሎት

የተሽከርካሪው ዓይነት

ብዛት

የጨረታው የሚዘጋበት ቀንና ሰዓት

ጨረታው ሚከፈትበት ቀንና ሰዓት

SREU/SC-003/2018

ሎት 1

የኤሌክትሪክ ካፕ ፒክአፕ

>5

ግንቦት 28/2018 ዓ.ም. ከቀኑ 8:30 ሰዓት

ግንቦት 28/2018 ዓ.ም. ከቀኑ 9:00 ሰዓት

ሎት 2

የኤሌክትሪክ አውቶሞቢል

>01 (እንደ አስፈላጊነቱ ይጨምራል)

ግንቦት 28/2018 ዓ.ም. ከቀኑ 8:30 ሰዓት

ግንቦት 28/2018 ዓ.ም. ከቀኑ 9:00 ሰዓት

  1. ማንኛውም በዘርፉ የተሰማራ የታደሰ ንግድ ሥራ ፈቃድ ያለው፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉበትን የታደሰ የንግድ ፈቃድ፤ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምስክር ወረቀት፤ የገንዘብ ሚኒስቴር የምዝገባ ምስክር ወረቀት እና የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር፣ ማስረጃ ያለው መሆን አለበት፤
  2. በጨረታው መሳተፍ ያለባቸዉ ተጫራቾች በዘርፉ የአቅራቢነት ማስረጃ ማቅረብ የሚችል መሆን አለበት፣ መልካም የሥራ አፈጻጸም ያለው እና ለዚሁ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል።
  3. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ማስታወቂያው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በድርጅታችን አካውንት ቁጥር 1000254328058(Shire District Connection Fee) የማይመለስ ብር 1,000.00 (አንድ ሺ) ገቢ በማድረግ ዘወትር በሥራ ስዓት አድራሻ፡- ሽረ ከተማ ግደይ ጋንዴ ሆቴል አጠገብ ህንፃ ላይ የሚገኘው የሽረ ሪጅን - ኤሌክትሪክ አገልግሎት ፅ/ቤት 3ኛ ፎቅ ሳፕላይ ቼይን ንብረትና ጠቅላላ አገልግሎት ቢሮ ቁጥር 20፣ በመምጣት የጨረታ ሰነድ መውሰድ ይችላሉ።
  4. ተጫራቾች ለ120 ቀናት እና ከዚያ በላይ ፀንቶ የሚቆይ የጨረታ ማስከበሪያ የሚያቀርቡት "ለሽረ ሪጅን ኤሌክትሪክ አገልግሎት" (SHIRE REGION ELECTRIC UTILITY) ተከፋይ የሆነ የገንዘብ መጠኑ ሎት1 ብር 30,000.00 (ሠላሳ ሺህ ብር) እንዲሁም ሎት2 ብር 10,000.00 (አሥር ሺህ ብር) በታወቀ ባንክ የተረጋገጠ ቼክ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ጋራንቲ መሆን ይኖርበታል።
  5. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ኦሪጅናል እና ኮፒ በማለት በተለያየ ፖስታ በማሸግ በአንድ ፖስታ በማድረግ ጨረታ ቁጥሩ SREu/SC-003/2018 የሚል ምልክት በማድረግ እስከ ግንቦት 28/2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ድረስ ከላይ በተጠቀሰው አድራሻ ቢሮ ቁጥር 20 ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፤
  6. ጨረታው ከላይ በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት ተዘግቶ በተመሳሳይ ቀን ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከቀኑ 9፡00 ሰዓት ላይ ይከፈታል፣
  7. ተቋሙ የተሻለ አማራጭ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፣
  8. ተጫራቾች ተጨማሪ መረጃ ከፈለጉ በስስክ ቁጥር +251 34 244 0237 መደወል ይችላሉ።

የሽ/ ሪጅን ኤሌክትሪክ አገልግሎት