Ethiopian Red Cross Society Tigray Branch

ቁጥር 139036,33

ቀን 09/08/2017

የጨረታ ማስታወቅያ

በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማሕበር የትግራይ ክልል ቅ/ጽ/ቤት በቀረበው ስፔስፊኬሽንና ከዚህ ጋር በተያያዘው ዝርዝር መሰረት ለመቐለ ዓዲ ግራትና ሽረ ከተሞች በERCSICRC Cooperation የበጀት ድጋፍ የኣምቡላንስ ጥሪ ማእከል ዕቃዎች (Office Equipment including Furniture & IT Equipment) በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡

ስለሆነም በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች

1. የዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላችሁ

2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ማረጋገጫ ማቅረብ የምትችሉ

3. የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) የተመዘገባችሁ

4. በአቅራቢነት የተመዘገባችሁ

5 የማይመለስ ብር 100.00 በመክፈል የጨረታ ሰነድ ከቢሮኣችን ግዢ ክፍል በስራ ሰዓት ከ 09/08/2018 ዓ/ም እስከ 23/08/2018 ዓ/ም መውሰድ ትችላላችሁ

6. ተጫራቶች የዋጋ ማቅረቢያ ሰነድ በትክክል ሞልታችሁ በማሸግ እስከ 26/08/2018 ዓ/ም 8፡00 ሰዓት ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀ ሳጥን ማስገባት ይቻላል፡፡ በተጨማሪም ለውድድር ለጨረታ ያቀረባቹሁት ዋጋ ለምን ያህል ጊዜ እንደሚቆይ /validity period መጠቀስ አለበት፡፡

7. ተጫራቶች አስፈላጊ የሆኑ ሰነዶች በታሸገ ፖስታ ማቅረብ አለባችሁ

8. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ 2%) ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡ በጥፊ ገንዘብ ማስያዝ ኣይፈቀድም፡፡

9. የጨረታ ሰነድ የሚከፈትበት ቀን 26/08/2018 ዓ/ም ከቀኑ 9፡00 ሰዓት ሲሆን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ጨረታው በሚከፈትበት ቀንና ሰዓት ቢገኙ ይመረጣል፡፡ ሆኖም ግን ባለመገንኘታቸው ጨረታው አይስተጓገልም፡፡

10. ጨረታ ኣሸናፊ የሆነ ኣቅራቢ የጨረታ ውጤቱ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ ውል በማሰር በኣምስት የስራ ቀናት ውስጥ ንብረት ማቅረብ ይኖርበታል፡፡

11. ጽ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፤፤

በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማሕበር የትግራይ ክልል ቅ/ጽ/ቤት ለተጨማሪ ማብራሪያ፡- በስልክ ቁጥር -- 0914027933/0914199979 መደወል ይችላል፡