የጨረታ ማስታወቂያ
ጨረታ ቁጥር፦ DBG/ICT/ERP/001/2026
ቀን 21/06/ 2018 ዓ.ም
ደስታ ቢዝነስ ግሩፕ የንግድ ስራውን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ለመደገፍ እና የአሰራር ቅልጥፍናን ለመጨመር፣ የተቀናጀ የኢንተርፕራይዝ ሪሶርስ ፕላኒንግ (ERP) ሲስተም ለመዘርጋት ይፈልጋል። በመሆኑም በዘርፉ በቂ ልምድ እና ብቃት ያላቸው ድርጅቶች በጨረታው ተሳታፊ እንዲሆኑ ይጋብዛል።
1. የሥራው ዝርዝር
• ለድርጅቱ ተስማሚ የሆነ የERP ሶፍትዌር ከፕሮጀክት ሰነዶች ማቅረብ
• ሲስተሙን ከድርጅቱ አሰራር ጋር ማጣጣም (Configuration & Customization)
• መረጃዎችን ከነባር ሲስተሞች ወደ አዲሱ ሲስተም ማዛወር (Data Migration) ለተጠቃሚዎች እና ለቴክኒክ ባለሙያዎች ስልጠና እና መመሪያዎች (User Manuals) መስጠት የተጠቃሚ
• ሲስተሙ ሙሉ በሙሉ ወደ ስራ ከገባ በኋላ ለሚከታተሉት 12 ወራት (1 ዓመት) ያለምንም ተጨማሪ ክፍያ የቴክኒክ ድጋፍ እና የጥገና አገልግሎት መስጠት
• አቅራቢው በየሦስት ወሩ (Quarterly) የሲስተሙን ደህንነት እና ጤንነት የመፈተሽ እና የዳታ ባክአፕ (Backup) በትክክል መስራቱን የማረጋገጥ ግዴታ ይኖርበታል።
• ሲስተሙ በተግባር እንዴት እንደሚሰራ ለድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች እና ለአይሲቲ ቡድን ማሳየት (presentation)
2. ተጫራቾች መሟላት ያለባቸው መስፈርቶች
ተጫራቾች የሚከተሉትን ህጋዊ እና ቴክኒካዊ ማስረጃዎች ማቅረብ ይኖርባቸዋል፦
• የ2018 ዓ.ም የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የቫት (VAT) ምዝገባ ሰርቲፊኬት
• የቲን (TIN) ቁጥር እና የዘመኑ የግብር ክሊራንስ ማቅርብ የሚችል
• ባለፉት 5 ዓመታት ውስጥ ቢያንስ 3 ተመሳሳይ የERP ተከላ ስራዎችን በታዋቂ ድርጅቶች ውስጥ ያከናወኑበት ምስክር ወረቀት (Experience certification) ማቅርብ የሚችል
• የሚቀርበው ሶፍትዌር አምራች (Vendor) እውቅና ያለው ወኪል ወይም አጋር (Certified Partner) መሆናቸውን የሚያሳይ ኣገልግሎት ዘመን የሚግልጽ ማስረጃ ማቅርብ የሚችል
• ተጫራቾች የሚያቀርቡት ፕሮፖዛል በድርጅታችን የተዛጋጅው RFP ሰነዱ ላይ የተጠቀሱትን የለድርጅቱ ፍላጎቶች በዝርዝር መመለሱን ማረጋገጥና ፕሮጀክቱ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ያለውን የጊዜ ሰሌዳ ማሳየት የሚችል
• ተጫራቾች የሚያቀርቡት የዋጋ ዝርዝር በድርጅቱ የፍላጎት ሰነድ (RFP) ላይ በተገለጹት ሞጁሎች (Module-based price) መሠረት (ለምሳሌ፦ ፋይናንስ፣ ንብረት አስተዳደር፣ የሰው ኃይል እና ደመወዝ፣ ሽያጭ እና ግዢ ወዘተ) የሚያስፈልገው የላይሰንስ ክፍያ፣ የተከላ ወጪ (Implementation) እና የስልጠና ወጪ በግልጽ ተለይቶ መታየት በዝርዝር መቅረብ ይኖርበታል
• ተጫራቾች ፕሮፖዛላቸውን ካስገቡ በኋላ በተወሰነ ቀን ቀርበው ለግምገማ ኮሚቴው ገለጻ ማድረግ ግዴታ ይኖርባቸዋል
3. የጨረታ ሰነድ አቀራረብ እና መረከቢያ
• ተጫራቾች የማይመለስ ብር 200 (ሁለት መቶ) በባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000271779767 በመክፈል ዝርዝር መመሪያውን (RFP) ከዋና መሥሪያ ቤት መውሰድ ይችላሉ
• ተጫራቾች የቴክኒክ እና የፋይናንስ ፕሮፖዛላችሁን በሁለት ለይታችሁ ማቅረብ ያለባችሁ ሲሆን፤ የቴክኒክ ፕሮፖዛሉን ያለ ይለፍ ቃል በPDF ፋይል በኢሜይል፣ የፋይናንስ ፕሮፖዛሉን ደግሞ በይለፍ ቃል የታሸገ PDF በኢሜይል በማያያዝ ወይም በታሸገ ኤንቨሎፕ በድርጅቱ ዋና መሥሪያ ቤት በአካል ቀርባችሁ ማስረከብ የምትችሉ ሲሆን፣ የኢሜይል ፋይሉ መክፈቻ የይለፍ ቃል (Password) የሚጠየቀውም የቴክኒክ ግምገማውን ማለፋችሁ ሲረጋገጥ ብቻ ይሆናል
• የጨረታ ማስከበሪያ (Bid Bond)፦ ተጫራቾች ለጨረታው ዋስትና የሚሆን ብር 200,000 (ሁለት መቶ ሺህ) በደስታ በርሀ ወሉ ስም የተዘጋጀ ሲፒኦ (CPO) ወይም ቅድመ ሁኔታ የማይጠይቅ የባንክ ዋስትና (Bank Guarantee) ማቅረብ ይኖርባቸዋል
• መቀበያ ኢሜይል: procurement@destabusinessgroup.com
4. ቀናት
• የመዝጊያ ቀን፦ 30/06/2018 ዓ/ም
• የማሳያ (Presentation) 03/07/2018 ዓ/ም
➢ ቦታ፦ ደስታ ቢዝነስ ግሩፕ ዋና መሥሪያ ቤት መቐለ ዓዲ ሓቂ ክ/ከተማ አስተዳደር በስተጀርባ
5. ማሳሰቢያ
• ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው
• የጨረታው ተሳትፎ እና ክፍያ በኢትዮጵያ ብር (ETB) ብቻ የሚፈጸም ይሆናል። ተጫራቾች ጨረታውን ካሸልፉበት ቀን ጀምሮ ከ 5-10 ቅናት ዉስጥ ወደሙሉ ትግበራ መጀምር ኣለባቸው
• ጨረታው ለ 10 ተክታታይ ቀንናት ከቀን እስክ30/06/2018 ዓ/ም የሚቆይ ይሆናል
• ጨረታው በቀን 30/06/ /2018 ዓ/ም 11:30 ተዘግቶ በቀን 04/07/2018 ዓ/ም 4:00 ሰዓት ተጫራቶጭችና ህጋዊ ወኪሎች ባሉብት ይክፈታል
ተጨማሪ መረጃ፦
• ስልክ፦ +251714003778/+251930 001630