https://tenders.milkta.com/am/tenders/display/8961
የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ ከዚህ በታች የተጠቀሱትን የተለያዩ ዕቃዎችና አገልግሎቶች ማለትም፡ ፖሊትዩን ትዩፕ፣ ጋብዮን፣ የማር ሰም፣ የላቦራቶሪ እቃዎች፣ የእንስሳት መድኃኒት፣ የእንስሳት መድኃኒት መገልገያ መሣሪያዎች ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል
  • የተለቀቀበት ቀን: ቀዳም ጥቅምቲ 8, 2012 (ከ 6 ዓመታት)
  • መዝግያ ቀን: ዓርቢ ጥቅምቲ 21, 2012 03:29 ጥዋት (ተዘጋ)
  • የጨረታ ማስከበርያ ዋጋ:00
  • ቦታ:መቐለ
  • የጨረታ ደኩመንት ዋጋ:100
  • ጨረታ ሚከፈትበት ቀንና ሰዓት: ዓርቢ ጥቅምቲ 21, 2012 03:30 ጥዋት
  • ምድብ: ህንፃ መሳርሒ/ ፍዮሪን ሆልቲካልቸር/ ፖልትሪ ቢ ኣኒማል ሃስባንድሪይ/ ላብራቶሪይን መሳሪሒታተ/ ናይ እንስሳት ምድሃኒታትን መሳሪሕታትን/ ቱቦታትን ኣክሰሰሪታትን/ ጥዕና ተንከፍ አቁሑትን ኣክሰሰሪ/ ሰራሕቲ ሓፂነ መፂን/
  • ሎት 1 ፖሊትዩን ትዩፕ፣ 
  • ሱት 2 ጋብዮን፣ 
  • ሱት 3. የማር ሰም፣ 
  • ሱት 4. የላቦራቶሪ እቃዎች፣ 
  • ሱት 5. የእንስሳት መድኃኒት፣ 
  • ሱት 6. የእንስሳት መድኃኒት መገልገያ መሣሪያዎች ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል:

በመሆኑም በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ በዘርፉ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላችሁ አቅራቢ ድርጅቶች በጨረታው እንድትሳተፉ እየጋበዝን፤ የተዘጋጀው የጨረታ ዶኩሜንት ለእያንዳንዱ የማይመለስ ብር 100.00 በመከፈል ጀምሮ ሕጋዊ የንግድ ፈቃዳችሁን በመያዝ ከቢሮአችን የዕቃ ግዥ ክፍል ቢሮ ቁጥር 12 በሥራ ሰዓት እየመጣችሁ መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን፤ በጨረታው ለመሳተፍ ቀጥለው የተዘረዘሩትን ማሟላት ያስፈልጋል:: 

  • የዘመኑ የታደሰ ንግድ ፈቃድ፣ የአቅራቢዎች ምዝገባ ሰርተፊኬት፣ የVAT ሠርቲፊኬት፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር(TIN) እና ያለፈው ወርቫት (VAT) ዲክለር የተደረገበት ማስረጃ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አብሮ መቅረብ አለበት:: 
  • ተጫራቾች የጨረታ መመሪያውን በጥንቃቄ አይተው መወዳደር አለባቸው። 
  • የጨረታ ማስከበሪያ ቢድ ቦንድ በጨረታ ዶክመንቱ ላይ የተጠቀሰውን መጠን ገንዘብ በ(CPO) አሠርተው ጨረታው ከመከፈቱ በፊት አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል:: ቢሯችን በጨረታ ከቀረበው የዕቃዎች ብዛት እስከ 20% የመጨመር ወይም የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው። 
  • ጨረታው ጥቅምት 21/2012 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡30 ሰዓት ተዘግቶ ወዲያውኑ መገኘት የሚፈልጉ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በቢሮአችን የዕቃ ግዥ ከፍል ይከፈታል። 
  • ቢሯችን የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታው ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። 

ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥሮች 034 440 36 63/034 440 43 46 ወይም በፋክስ ቁጥር 034 440 99 71/034 440 36 63 መጠየቅ ይቻላል፡፡ 

የትግራይ ክልል ግብርናና 

ገጠር ልማት ቢሮ