https://tenders.milkta.com/am/tenders/display/7553
የትግራይ ልማት ማህበር የኤሌክትሮኒክስ እቃዎችና ጀኔረተር በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል
  • የተለቀቀበት ቀን: ሰንበት ጉንበት 18, 2011 (ከ 6 ዓመታት)
  • መዝግያ ቀን: ሰሉስ ሰነ 4, 2011 08:30 ከሰአት (ተዘጋ)
  • የጨረታ ማስከበርያ ዋጋ:የጨረታው ማስከበሪያ ብር የተለያየ ነው
  • ቦታ:መቐለ
  • የጨረታ ደኩመንት ዋጋ:100
  • ጨረታ ሚከፈትበት ቀንና ሰዓት: ሰሉስ ሰነ 4, 2011 09:00 ከሰአት
  • ምድብ: ኮምፒተርን ተዛመድቲ / ናይ ኮምፒተር ተዛመድቲ አቁሑትን/ ኤሌክትሪካልን መሳርሕታትን መለዋወጢን/ ኤሌክትሮኒክስ መሳርሕታትን መለዋወጢን/ ኤሌክትሮ-መካኒክስ ኣቁሑትን ግልጋሎትን/

 ኮምፒተር ማእከልና ለፅሕፈት ቤቱ አገልግሎት የሚውሉኮምፒተርና የኮምፒተር ተዛማጅ እቃዎችና ጀነረተር ማለት |-ዴስክቶፕ ኮምፒተር ብዛት 100 ፣ቲንክሌንት ብዛት 2300፣ ሞኒተር ብዛት2300፣ ኪቦርድ ብዛት 2300 ፣ ማውዝ ብዛት 2300፣ስተፕላይዘር ብዛት 100፣ ዲቫይደር ብዛት 1200 / ባለ 200 KVA ጉልበት ያለውጀኔረተር ብዛት 1 በሎት ደረጃ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል ::

1 የዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው ፣የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /Tin Number/ ሰርትፍኬትና የመጨረሻ ወር የቫትዲ ክላሬሽን የሚያቀርቡ
2 የዘመኑ የታደሰ የኣቅራቢነት የምዝገባ ሰርተፊኬት ማቅረብ የሚችሉና የቫት ተመዝጋቢ የሆኑ፣ 

3 ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ የተጠቀሱትን የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር ኣያይዘው ማቅረብ አለባቸው፣ 

4  ተጫራቾች አሸናፊ ሁነው ሲገኙ ውሉ ከታሰረበት በ60 ተከታታይ ቀናት የኤሌክትሮኒክ እቃዎቹና ጀኔረተር ማቅረብ የሚችሉ ተጫራቾች ለኤሌክትሮኒክስ 100,000.00 ለጀኔረተር 20,000.00 የኢትዮጵያ ብር የጨረታ ማስከበሪያ - በሲፒኦ ብቻ ማቅረብ ይኖርባቸዋል 

5  ተጫራቾች የጨረታው ሰነደቻቸውን በሁለት የተለያዩ ኤንቨሎፖች የቴክኒካል እና ፋይናንሻል ኦርጅናል ሰነዶች ለያይተውበማሸግ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።በተጨማሪም ከቴክኒክ እና ከፋይናንሻል ሰነድ አንድ አንድ ኮፒ በማሸግ - ፊርማና የድርጅቱማሕተም በማሳረፍ ማቅረብ ይኖርባቸዋል ፣

6 የጨረታው ሰነድ በሪፖረተር ጋዜጣ ከወጣ ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት ለኤሌክትሮኒክስና ጀኔረተር የማይመለስ ብር 100 (መቶ ብር) በመክፈል መቐለ በሚገኘው ትግራይ ልማት ማህበር ፅ/ቤት ከቢሮ ቁጥር 430 ወይም አዲስ አበባ ቦሌ መድሃኒአለም ፊትለፊት ፎቅ የሚገኘው ህድሞና ህንፃ ቢሮ ቁጥር 12 መውሰድ ይችላሉ፣

7 ይህ ጨረታ በማስታወቅያ በወጣ በ16ኛው ቀን በ8.30 ሰዓት ታሽጎ በዕለቱ 9.00 ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው ባሉበት በተጠቀሰው ቀን መቀሌ በሚገኘው የትግራይ ልማት ማህበር ዋና ፅ/ቤት ይከፈታል፣ 

8  አሸናፊዎች ያሸነፉት እቃዎች መቐለ በሚገኘው የትግራይ ልማት ማሕበር ዋና ፅ/ቤት ማድረስ ይጠበቅባቸዋል

9 አሰሪው ፅ/ቤት የተሻለ መንገድ ካገኘ በጨረታው አይገደድም::
ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር፧ -0344406944 መጠየቅ ይቻላል