https://tenders.milkta.com/am/tenders/display/5408
የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ የአይቲ ዕቃዎች (IT Equipment)፣ ኤሌክትሪክ ጀነሬተርና አነስተኛ የእጅ መሣሪያዎች፣ የእንሰሳት ሕክምና መገልገያ ዕቃዎች፣ የማንጎና የአቮካዶ ፍሬ በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል
  • የተለቀቀበት ቀን: ሶኒ ታሕሳስ 1, 2011 (ከ 7 ዓመታት)
  • መዝግያ ቀን: ሰሉስ ታሕሳስ 30, 2011 03:30 ጥዋት (ተዘጋ)
  • የጨረታ ማስከበርያ ዋጋ:ኣልተገለፀም
  • ቦታ:መቐለ
  • የጨረታ ደኩመንት ዋጋ: 100.00
  • ጨረታ ሚከፈትበት ቀንና ሰዓት: ሰሉስ ታሕሳስ 30, 2011 04:00 ጥዋት
  • ምድብ: ፍዮሪን ሆልቲካልቸር/ ኮምፒተርን ተዛመድቲ / ናይ ኮምፒተር ተዛመድቲ አቁሑትን/ ኤሌክትሮ-መካኒክስ ኣቁሑትን ግልጋሎትን/ ናይ መድሓኒት ምህርቲ/

የጨረታ ማስታወቂያ

ጨረታ ቁጥር TG/AGP-CU

 10/2011

የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ ከግብርና ዕድገት ፕሮግራም (AGP-II) በተገኘ በጀት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ዕቃዎች ማለትም፡-

  • ሎት 1. የአይቲ ዕቃዎች (IT Equipments)
  • ሎት 2. ኤሌክትሪክ ጀነሬተርና አነስተኛ የእጅ መሣሪያዎች
  • ሎት 3.  የእንሰሳት ሕክምና መገልገያ ዕቃዎች
  • ሎት 4.  የማንጎና የአቮካዶ ፍሬ

በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡

በመሆኑምበጨረታውላይለመሳተፍ  የምትፈልጉ  በዘርፉ  ሕጋዊ  ንግድ  ፈቃድ  ያላችሁ አቅራቢ ድርጅቶች በጨረታው እንድትሳተፉ እየጋበዝን የተዘጋጀው የጨረታ ዶክመንት ለእያንዳንዱ የማይመለስ ብር 100.00 /አንድ መቶ ብ/ በመክፈል ከታህሳስ 1 ቀን 2011 ዓ.ም ጀምሮ ከቢሮአችን የዕቃ ግዢ ንዑስ ሥራ ሂደት በሥራ ሰዓት እየመጣችሁ መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን በጨረታዉ ላይ ለመሳተፍ ቀጥለዉ የተዘረዘሩትን ማሟላት ይጠበቅባችኋል፡፡

  • የዘመኑ  የታደሰ የንግድ ፈቃድ የአቅራቢዎች ምዝገባ ሠርተፊኬት፣የቫት  ሰርተፈኬት፣ ያለፈዉ ወር ቫት ሪፖርት የተደረገበት ማስረጃ፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር (ቲን) ማስረጃ ፎቶ ኮፒ ከጨረታ ሰነዱ ጋር ተያይዞ መቅረብ አለበት፡፡
  • ተጫራቾች የጨረታ መመሪያውን በጥንቃቄ አይተው መወዳደርአለባቸው፡፡
  • የጨረታ ማስከበሪያ ቢድ ቦንድ በጨረታ ዶክመንቱ ላይ የተገለፀዉን መጠን በቢሯችን ስም በሲፒኦ አሠርተዉ ጨረታዉ ከመከፈቱ በፊት ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  • ቢሮአችን በጨረታ ከቀረበው የዕቃዎች ብዛት እስከ 15% ለመቀነስ ወይም ለመጨመር መብቱ የተጠበቀ ነዉ፡፡
  • ጨረታው ታህሳስ 30 ቀን 2011 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡30 ሰዓት ተዘግቶ በዚያዉ ዕለት በ4፡00 ሰዓት ላይ መገኘት የሚፈልጉ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በቢሮአችን የዕቃ ግዥ ንኡስ ሥራ ሂደት ይከፈታል፡፡
  • ቢሮአችን የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥሮች 0344-403663፣ 0344-404723 ወይም በፋክስ ቁጥር 0344-409971 መጠየቅ ይቻላል፡፡

የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ