https://tenders.milkta.com/am/tenders/display/5287
በትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የውሃ ሀብት ቢሮ የሚገኙ የውሃ ሞተሮች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
  • የተለቀቀበት ቀን: ዓርቢ ሕዳር 14, 2011 (ከ 7 ዓመታት)
  • መዝግያ ቀን: ሓሙስ ታሕሳስ 4, 2011 03:00 ጥዋት (ተዘጋ)
  • የጨረታ ማስከበርያ ዋጋ:10000
  • ቦታ:መቐለ
  • የጨረታ ደኩመንት ዋጋ:30
  • ጨረታ ሚከፈትበት ቀንና ሰዓት: ሓሙስ ታሕሳስ 4, 2011 03:10 ጥዋት
  • ምድብ: ኤሌክትሮ-መካኒክስ ኣቁሑትን ግልጋሎትን/ ቅፋሮ ማይ ኢንጂነሪንግ ማሺነሪ, ኣቁሑትን ኣክሰሰሪ/

1 ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ ከ 14/03/2011 ዓ.ም ጀምሮ የማይመለስ ብር 30 (ሰላሳ ብር) በመክፈል ከዚህ በታች ከተጠቀሱት አድራሻዎቻችን ማግኘት ይችላሉ፡፡

2 በትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የውሃ ሀብት ቢሮ ካፒታል ግዥ ክፍል

3 የጨረታ ሰነዶችን ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 የሥራ ቀናት ከታች በተገለጸው አድራሻችን በመቅረብ ማግኘት ይቻላል፡፡

4 ተጫራቾች የዘመኑን ግብር የከፈሉበት የታደሰ የንግድ ፈቃድ እንዲሁም የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN NUMBER) ምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡

5 ተጫራቾች ለውሃ ሞተሮች ፣100,000 ብር የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በባንክ የተረጋገጠ (CPO)ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡

6 ተጫራቾች የጨረታ ሰነዳቸውን፣ «በሁለት ፖስታ» «አንድ ኦርጅናል» እና ሁለት ኮፒ በሰም የታሸጉ ኤንቨሎፖች እስከ 4/4/2011 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት በፊት ከላይ በተጠቀሰው የጽ/ቤቱ አድራሻ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት አለባቸው፡፡

7 ጨረታው በተመሳሳይ ቀን በ4/4/2011 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡10 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በጽ/ቤቱ ቢሮ መደበኛ ግዥ ክፍል ይከፈታል፡፡ በተጨማሪ ተጫራቾች ስለ ጨረታው ማብራሪያ ከፈለጉ ስልክ ቁጥር፦0344411795/0344411794 በተጠቀሰው አድራሻ ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡

8 መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

9 የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የውሃ ሀብት ቢሮ ካፒታል ግዥ ክፍል