https://tenders.milkta.com/am/tenders/display/5205
የሰሜን ሪጅን ኢትዩ ቴሌኮም የተለያዩ ዕቃዎች ይዞ የመጣ የጣዉላ ሳጥን : አሮጌ ጣዉላ : ኬብሉ ናብረቱ የተፈታ ድራም ፣ ያገለገለ ጠረጴዛ፣ ያገለገለ ወንበር፣ እና የእንጨት ምሰሶ ባለበት ሁኔታ በግልፅ ጨረታ መሸጥ ይፈልጋል።
  • የተለቀቀበት ቀን: ሓሙስ ጥቅምቲ 29, 2011 (ከ 7 ዓመታት)
  • መዝግያ ቀን: ረቡዕ ሕዳር 12, 2011 08:00 ከሰአት (ተዘጋ)
  • የጨረታ ማስከበርያ ዋጋ:10000.00
  • ቦታ:መቐለ
  • የጨረታ ደኩመንት ዋጋ:50.00
  • ጨረታ ሚከፈትበት ቀንና ሰዓት: ረቡዕ ሕዳር 12, 2011 08:15 ከሰአት
  • ምድብ: ዕንፀይቲን ስራሕቲ ዕንፀይቲ/ ካልኦት ዝሽወጡ/ ዘገልገሉ ኣቅሑት መሸጣ/

ተጫራቾች ማሟላት ያለባቸው ነገሮች

1 ተጫራቾች የዘመኑ ግብር የከፈሉና የታደሰ የ2010 ዓ/ም ንግድ ፈቃድ ማቅረብ ይኖርባቸዋል

2 ተጫራቾች ለጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ በታወቀ በባንከ የተረጋገጠ ቼክ ወይም ስፒኦ ብር 10,000 ማስያዝ አለበት

3 ተጫራቾች ከ ጥቅምት 29 2011ዓ/ም ሎጀስቲክ እና ፋሲሊቲ ክፍል 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 402 በመምጣት የማይመለስ ብር /ሃምሳ ኣምስት/ 50.00 በመክፈል የጨረታ ሰነዱን ከገዙ በኃላ ለሽያጭ የተዘጋጁ ዕቃዎችን አዋሽ የእህል መጋዘን አጠገብ በሚገኘዉ መጋዝን ዉስጥ ለጨረታ የተዘጋጀዉ ዕቃዎችን በኣካል ቦታዉ ድረስ በመሄድ በስራ ሰዓት ማየት ይቻላል።

4 ተጫራቾች ዕቃዎቹን የሚገዙበት የኣንዱ ዋጋ ያለ ቫቱ 15% በማስቀመጥ በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ አዘጋጅተዉ ሙሉ አድራሻቸዉ በመግለፅ ሎጂስቲክ እና ፋሲሊቲ ክፍል 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 402 ያዘጋጀዉ የጨረታ ሳጥን ጥቅምት 29 ቀን 2011  ዓ/ም እስከ ህዳር 12 ቀን 2011 ዓ/ም ከቀኑ 8:00 ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል። ከዚህ በኃላ የሚቀርበዉ ማንኛዉም ሰነድ ተቀባይነት የለውም።

5 ጨረታዉ ፍላጎት ያላቸዉ ተጫረቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት ሕዳር 12 ቀን 2011 ዓ/ም  ከቀኑ 8:15 በሰሜን ሪጅን ኢትዩ ቴሌኮም 5ኛ ፎቅ የሚገኘዉ የስብሳባ አዳራሽ ይከፈታል።

6 አሸናፊዉ ተጫራቾች ላሸነፈዉ ዋጋ 15% ቫትን ጨምሮ ገቢ ካደረገ በኃላ በአምስት /5/ የስራ ቀናት ዉስጥ ለጨረታ ተለይቶ የተዘጋጁ  አሮጌ ጣዉላ : የጣዉላ ሳጥን :  ኬብሉ ና ብረቱ የተፈታ ድራም ብቻ  በስራ ሰዓት ማንሳት ኣለባቸው። ሆኖም ግን  በጊዜ ገደብ ካላነሱ ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት ስፒኦ ተደርጎ ሪጅኑ የራሱን አማራጭ ይወስዳል።

7 ዕቃዎቹ በሙሉ ካልሆነ በከፊል መጫረት ኣይችሉም።

8 መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ

9 አንድ ተጫራች ባቀረበዉ ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ አይቻልም

ስልክ ቁጥር 0344-413134