https://tenders.milkta.com/am/tenders/display/5095
የየትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ ጋብዮን፣ የእርሻና ችግኝ ጣቢያ መገልገያ መሣሪያዎች፣ የጽህፈት መሣሪያዎች፣ የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች፣ ሕትመት፣ የጽዳት እቃዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል
  • የተለቀቀበት ቀን: ሰሉስ ጥቅምቲ 13, 2011 (ከ 7 ዓመታት)
  • መዝግያ ቀን: ሓሙስ ጥቅምቲ 29, 2011 03:30 ጥዋት (ተዘጋ)
  • የጨረታ ማስከበርያ ዋጋ:0
  • ቦታ:መቐለ
  • የጨረታ ደኩመንት ዋጋ:100
  • ጨረታ ሚከፈትበት ቀንና ሰዓት: ሓሙስ ጥቅምቲ 29, 2011 03:31 ጥዋት
  • ምድብ: ህንፃ መሳርሒ/ ፍዮሪን ሆልቲካልቸር/ ናይ ንፅህናን ፅሬት ኣቁሑት/ ኮንስትራክሽን ጥረ ኣቁሑት/ ኤሌክትሮኒክስ መሳርሕታትን መለዋወጢን/ ናይ ፅሕፈት መሳሪሕታተት/ ናይ ሕትመት ስራሕቲ/

የየትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ ከዚህ በታች የተጠቀሱት የተለያዩ ዕቃዎችና አገልግሎቶች ማለትም፡-

ሎት 1 ጋብዮን

ሎት 2 የእርሻና ችግኝ ጣቢያ መገልገያ መሣሪያዎች

ሎት 3 የጽህፈት መሣሪያዎች

ሎት 4 የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች

ሎት 5 ሕትመት

ሎት 6 የጽዳት እቃዎች

በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ቁጥር 027/2011 ዓ.ም ወጥቶ በአዲስ ዘመን ቁጥር 030/2011 ዓ.ም በተደረገው ማስተካከያ መሠረት በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፤ በመሆኑም በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ በዘርፉ ሕጋዊ የንግድ ፍቃድ ያላችሁ አቅራቢ ድርጅቶች በጨረታው እንድትሳተፉ እየጋበዝን፣ የተዘጋጀው የጨረታ ዶክሜንት ለእያንዳንዱ የማይመለስ ብር 100.00 በመክፈል ጀምሮ ሕጋዊ የንግድ ፈቃዳችሁን በመያዝ ከቢሮአችን የዕቃ ግዥ ክፍል ቢሮ ቁጥር 12 በሥራ ሰዓት እየመጣችሁ መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን፣ በጨረታው ለመሳተፍ ቀጥለው የተዘረዘሩትን ማሟላት ያስፈልጋል።

  • የዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የአቅራቢዎች ምዝገባ ሰርተፊኬት፣ የVAT ሰርተፊኬት፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር (TIN) እና ያለፈው ወር ቫት (VAT) ዲክለር የተደረገበት ማስረጃ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አብሮ መቅረብ አለበት።

    ተጫራቾች የጨረታ መመሪያውን በጥንቃቄ አይተው መወዳደር አለባቸው።
  • የጨረታ ማስከበሪያ ቢድ ቦንድ በጨረታ ዶክመንቱ ላይ የተጠቀሰው መጠን ገንዘብ በCPO አሰርተው ጨረታው ከመከፈቱ በፊት አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
  • ቢሮአችን በጨረታ ከቀረበው የዕቃዎች ብዛት እስከ 20% የመጨመር ወይም የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው።
  • ጨረታው ጥቅምት 29 ቀን 2011 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡30 ሰዓት ተዘግቶ ወዲያውኑ መገኘት የሚፈልጉ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በቢሮአችን የዕቃ ግዥ ክፍል ይከፈታል።
  • ቢሮአችን የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታው ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

    ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥሮች 0344403663/0344404346 ወይም በፋክስ ቁጥር 0344409971/0344403663 መጠየቅ ይቻላል።

የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር