https://tenders.milkta.com/am/tenders/display/4992
በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የማዕከላዊ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ የግንባታ ዕቃዎች፣ የኤሌክትሪክ ዕቃዎች፣ የባህር ዛፍ አጣና፣ ድንጋይ፣ አሸዋና ጠጠር፣ ብሎኬት፣ አቡጀዴና ሻሽ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል
  • የተለቀቀበት ቀን: ዓርቢ መስከረም 25, 2011 (ከ 7 ዓመታት)
  • መዝግያ ቀን: ሶኒ ጥቅምቲ 5, 2011 04:00 ጥዋት (ተዘጋ)
  • የጨረታ ማስከበርያ ዋጋ:00
  • ቦታ:መቐለ
  • የጨረታ ደኩመንት ዋጋ:200
  • ጨረታ ሚከፈትበት ቀንና ሰዓት: ሶኒ ጥቅምቲ 5, 2011 04:30 ጥዋት
  • ምድብ: ህንፃ መሳርሒ/ መኽዝን/ ኮንስትራክሽን ጥረ ኣቁሑት/ ኤሌክትሪካልን መሳርሕታትን መለዋወጢን/ ጨርቃ መርቂን ኣልባሳትን/
  1. የግንባታዕቃዎች
  2. የኤሌክትሪክዕቃዎች
  3. የባህርዛፍአጣና
  4. ድንጋይ፣አሸዋናጠጠር
  5. ብሎኬት
  6. አቡጀዴናሻሽ

1 ተጫራቾች ለሚጫረቱባቸው የጨረታ አይነቶች ህጋዊ የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያላቸው በአቅራቢነት ስለመመዝገባቸው የአቅራቢነት ምዝገባ የምስክርነት ወረቀት ማቅረብ የሚችሉና የዘመኑን ግብር መክፈላቸውን ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችሉ፡፡

2 የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ /ከፋይነት / ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችሉ፡፡

3 የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችሉ፡፡

4 ተጫራቾች ለሚጫረቱባቸው ለእያንዳንዱ ጨረታ የጨረታ ማስከበሪያ በጨረታ ሰነዱ ላይ በተገለፀው መመሪያ መሰረት በባንክ የተረጋገጠ CPO ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡

5 ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ዋጋ በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ የዕቃውን አይነት ኤንቨሎፑ ላይ በግልፅ መፃፍ ይኖርባቸዋል፡፡

6 የጨረታ ሰነዱን ከተጫራቾች ዝርዝር መመሪያ ጋር የማይመለስ ብር200.00 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ታውጆ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ ባሉት ቀናት ውስጥ ሽሬ እደሥላሴ በሚገኘው የማዕከላዊ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ ግዥ ቡድን ቢሮ መግዛት ይቻላል፡፡

7 ተጫራቾች የጨረታ ሰነዳቸውን ሽሬ ከተማ በሚገኘው ማ/ዕዝ ጠ/መምሪያ መዝናኛ ክበብ ውስጥ ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡

8 ጨረታውጥቅምት 5 ቀን 2011 ዓ.ም ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት ላይ ተዘግቶ በዕለቱ 4፡30 ሰዓትተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ማ/ዕዝ መዝናኛ ክበብ ውስጥ ይከፈታል፡፡

9 አሸናፊ ተጫራቾች ውል ሲፈፅሙ የመልካም ስራ አፈፃፀም ዋስትና በባንክ የተረጋገጠ CPO ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡ ያሸነፉበትን ዕቃ በራሳቸው ወጭ በማጓጓዝ እና በማራገፍ ሽሬ እንደሥላሴ ከተማ በሚገኘው የማዕከላዊ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ ግምጃ ቤት ማስረከብ ይጠበቅባቸዋል፡፡

10 መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ እንዲሁም 20% ጨምሮ ወይም ቀንሶ የመግዛት መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 034-444-23-77 / 034-444-43-93 ይደውሉ።