https://tenders.milkta.com/am/tenders/display/4299
የሰሜን ሪጅን ኢትዩቴሌኮም የተለያዩ ዕቃዎች ይዞ የመጣ የጣዉላ ሳጥን : አሮጌ ጣዉላ : ብረቱን ኬብሉ የተፈታ ድራም ያገለገለ ጠረጰዛ :ያገለገለ ወንበር እና የእንጨት ምሰሶ ባለበት ሁኔታ በግልፅ ጨረታ መሸጥ ይፈልጋል
  • የተለቀቀበት ቀን: ዓርቢ መጋቢት 21, 2010 (ከ 8 ዓመታት)
  • መዝግያ ቀን: ሶኒ ሚያዝያ 1, 2010 08:00 ከሰአት (ተዘጋ)
  • የጨረታ ማስከበርያ ዋጋ:10000
  • ቦታ:መቐለ
  • የጨረታ ደኩመንት ዋጋ:50
  • ጨረታ ሚከፈትበት ቀንና ሰዓት: ሶኒ ሚያዝያ 1, 2010 08:15 ከሰአት
  • ምድብ: ዕንፀይቲን ስራሕቲ ዕንፀይቲ/ ካልኦት ዝሽወጡ/ ዘገልገሉ ኣቅሑት መሸጣ/

1 ተጫራቾች የዘመኑ ግብር የከፈሉና የ2010 ዓም የታደሰ ንግድ ፈቃድ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል

2 ለጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ በታወቀ በባንከ የተረጋገጠ ቼክ ወይም ስፒኦ ብር 10,000 ማስያዝ አለበት

3 ተጫራቾች ከ መጋቢት 19 ቀን 2010 ዓም ሎጀስቲክ እና ፋሲሊቲ ክፍል 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 402 በመምጣት የማይመለስ ብር /ሃምሳ ኣምስት/ 50 በመክፈል የጨረታ ሰነዱን ከገዙ በሃላ ለሽያጭ የተዘጋጁ ዕቃዎችን ዋናዉ ግምጃ ቤት ግቢ ዉስጥ እና አዋሽ የእህል መጋዘን አጠገብ በሚገኘዉ ጋራጅ ግቢ ቀበሌ 17 የከብቶች ገቢያ ተብሎ በተለምዶ በሚጠራዉ ቦታ እና ኩሃ ኢትዩ ቴሌኮም ግቢ ዉስጥ ለጨረታ የተዘጋጁ የተለያዩ ዕቃዎች በኣካል ቦታዉ ድረስ በመምጣት በስራ ሰዓት ማየት ይጠበቅባቸዋል

4 ተጫራቾች ዕቃዎቹን የሚገዙበት የኣንዱ ዋጋ ያለ ቫቱ 15% በማስቀመጥ በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ አዘጋጅተዉ ሙሉ አድራሻቸዉ በመግለፅ ሎጂስቲክ እና ፋሲሊቲ ክፍል 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር ያዘጋጀዉ የጨረታ ሳጥን መጋቢት 19 ቀን 2010 ዓም እስከ ሚያዝያ 1 ቀን 2010 ዓም ከቀኑ 8:00 ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል ከዚህ በኃላ የሚቀርበዉ ማንኛዉም ሰነድ ተቀባይነት

5 ጨረታዉ ፍላጎት ያላቸዉ ተጫረቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት ሚያዝያ 1 ቀን 2010 ከቀኑ 8:15 በሰሜን ሪጅን ኢትዩ ቴሌኮም 5ኛ ፎቅ የሚገኘዉ የስብሳባ አደራሽ ይከታል

6 አሸናፊዉ ተጫራቾች ላሸነፈዉ ዋጋ 15% ቫትን ጨምሮ ገቢ ካደረገ በኃላ በአምስት የስራ ቀናት ዉስጥ ለጨረታ ተለይቶ የተዘጋጁ የጣዉላ ሳጥን : አሮጌ ጣዉላ : ብረቱን ኬብሉ የተፈታ ድራም ያገለገለ ጠረጰዛ :ያገለገለ ወንበር እና የእንጨት ምሰሶ በተገለጸዉ የጊዜ በስራ ሰዓት ማንሳት አለባቸዉ አሸናፊዉ በጊዜ ገደብ ካላነሱ ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት ስፒኦ ተደርጎ ሪጅኑ የራሱን አማራጭ ይወስዳል

7 ዕቃዎቹ በሙሉም ወይም በከፊል መጫረት ይችላሉ

8 መ/ቤቱ የተሻላ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ

9 አንድ ተጫራች ባቀረበዉ ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ አይቻልም

ስልክ ቁጥር 0344413134