https://tenders.milkta.com/am/tenders/display/17354
የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ለ2017 ዓ/ም በጀት ዓመት የትምህርት ዘመን የተጋገረ የዳቦ አቅርቦት በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል
  • የተለቀቀበት ቀን: ረቡዕ ጉንበት 27, 2017 ( ከ 9 ወር)
  • መዝግያ ቀን: ሰሉስ -18, 1745 06:00 ከሰአት (ተዘጋ)
  • የጨረታ ማስከበርያ ዋጋ:250,000.00
  • ቦታ:ዓዲግራት
  • የጨረታ ደኩመንት ዋጋ:200.00
  • ጨረታ ሚከፈትበት ቀንና ሰዓት: ሰሉስ -18, 1745 06:00 ከሰአት
  • ምድብ: ኣቅርቦት ምግቢ /

ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ

የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ለ2017 ዓ/ም በጀት ዓመት የትምህርት ዘመን የተጋገረ የዳቦ አቅርቦት በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡

በዚሁ መሰረት፡-

  1. በዘርፉ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያለውና ፍቃዱንም በዘመኑ የታደሰ መሆኑ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል ፣
  2. በቀረበው ዝርዝር ስፔስፊኬሽን መሰረት ማቅረብ የሚችል፣
  3. ተጫራቹ ቲን ሰርተፊኬት ምዝገባ ማቅረብ የሚችል፣
  4. ተጫራቹ የማቅረቢያ መታወቂያ ምዝገባ ያለው መሆኑ ማቅረብ የሚችል፣ ሎት 1 የተጋገረ ዳቦ አቅርቦት፣ የጨረታ ማስከበሪያ 250,000.00 ብር በሲፒኦ ወይም በባንክ ጋራንቲ ማቅረብ የሚችል፣
  5. ማንኛውም ተጫራች የማይመለስ 200.00 ብር /ሁለት መቶ ብር /በመክፈል የጨረታ ሰነዱ መግዛት ይችላል፣
  6. ማንኛውም ተጫራች በእያንዳንዱ የጨረታ ሰነድ ማህተምና ፊርማ በማድረግ ማቅረብ አለበት፣
  7. ጨረታው ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮበ16 ኛው ቀን በስራ ሰዓት ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በተመሳሳይ ቀን በ 4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎች በተገኙበት ይከፈታል፣
  8. ዩኒቨርሲቲው ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር፡- 09 14 70 31 20 ደውሎ ማነጋገር ይቻላል።